Friday, October 31, 2014

ፕሬስ በዘመነ ወያኔ

ፕሬስ(Press) ራሱን ለመግለጥ ከተፈቀደለትና ከተመቻቸለት መንግሥት አገርን በአግባቡ እንዲመራ የሚያግዝ ታላቅ የመርጃ መሣሪያ እንጂ ፀረ-መንግሥት አቋምም ሆነ ሚና የለውም። ፕሬስ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን አስተዋጽዖ ከማድረጉም በላይ፤ የመንግሥትንም ሆነ የድርጅቶችን፤የግለሰቦችንና የአጠቃላይ ዜጎችን በጎ ጎን በማጉላት ለሕብረተሰቡ ይፋ በማድረግ ከፍተኛ ድርሻ አለው። ከብዙ በጥቂቱ ነጻ ፕሬስ ሙስናንና ስግብግብነትን በመዋጋት ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ያጋልጣል፥የሕዝብን የበላይነት ያስረጋግጣል፥ እንዲሁ የሥልጣን ክፍፍልንና ሕዝባዊ የፖለቲካ ተሳትፎን ያዳብራል። ከዚህም ባሻገር በሥልጣን ላይ ያለው መንግስት የአገሪቱ ሕገ መንግስ በሚደነግገው መሰረት ሕዝብን ያለምንም አድልዎና በደል እያስተዳደረ መሆን አለመሆኑን ለሕዝብ ያስተጋባል። የፕሬስ አገልግሎት ላወቀበትና በአግባቡ ለተረዳው አወንታዊው አስተዋጽኦ ብቻ ሳይሆን አሉታዊውና ነቀፋው እንኳን ሳይቀር ገምቢ ነው። ስህተትን እየጠቆመ፥ጠማማውን እያቀና መንግሥትንም ቢሆን ለአስተዳደር ጥራት ያሰናዳል እንጂ አንድም ጉዳት የለበትም።  

ስለዚህ ፕሬስ ማለት የሕዝብን ሰብአዊ መብቶች በአግባቡ እየጠበቀ የሚያስጠብቅ  የወቅቱን ፖለቲካዊና ምጣኔ ሀብታዊ እውነትና ሂደት እየተከታተለ ለሕዝብ የሚያቀርብና ለዲሞክራዊ እድገት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ተግባራዊ ተቋም ነው። እንዲህ ያለው ነባርዊ ሐቅ ለወያኔዎች ባይዋጥላቸውም ቅሉ፤ የተባለለትም ሆነ የሚባልለት ሁሉ የፕሬስን የከበረ ዋጋ የሚመጥን አይደለም።

Thursday, October 23, 2014

መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ



 ‹ ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ሰው ሆኖ ለእስር ይወጣል››
‹‹ተመስገን፣ የህዝብ ልጅ ነው፤ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ‹‹ስለተመስገን ደሳለኝ ሃሳቤን አስተላልፍልኝ›› ካለኝ የተወሰደ
ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ዕለት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆነውን አቶ አንዷለም አራጌን በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ላገኛቸው ችዬ ነበር – ለአቤል አለማየሁ ጋር፡፡ ባለፈው ሳምንት የ‹‹ባንዲራ ቀን››     በተከበረበት ዕለት ቃሊቲ ከወዳጄ እዩኤል ፍስሐ ጋር ሄጅ እነስክንድርን መጠየቅ ሳንችል ተመልሰን ነበር። 

Tuesday, October 21, 2014

ኤልያስ ገብሩ ዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተጠራ



ደስ ባለው ጊዜ ክስ የሚቀሰቀስ መንግሥት
እንግዲህ፣ ‹‹ማዕከላዊ ናና ክስህን ውሰድ›› ተብያለሁ

ከቀኑ አስር ሰዓት ላይ ሞባይል ስልኬ አቃጨለች፡፡ ከጎኔ ወዳጄ አቤል አለማየሁ ነበር፡፡ የመስመር ስልክ ነው፡፡ አነሳሁት፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ›› የሚል የሴት ድምጽ አደመጥኩ፡፡ ‹‹አዎን›› በማለት መለስኩላት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ መስመር ላይ ጠብቅ›› አለችኝ፡፡

ወዲያው አንድ ወንድ አነሳና ሰላምታ ሰጥቶ አናገረኝ፡፡ የሚደውለው ከፌዴራል ፖሊስ መሆኑን ጠቆመኝና ‹‹ባለፈው ተቋርጦ የነበረው ክስህ ስለተዘጋጀ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ቁጥር 76 መጥተህ ውሰድ›› አለኝ፡፡ ስለጉዳዩ ጥቂት ቃላቶች ተለዋወጥን፡፡ 

Friday, October 17, 2014

ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ


ከደቡብ ኅብረት ፕሮፌሰር በየነ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል


ምርጫ ቦርድ በጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ “ጥያቄዎቻችን የሚመልስ አይደለም” በሚል የሰማያዊ ፓርቲ ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በተጨማሪም የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ) እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በትናንትናው ዕለት ከምርጫ 2007 ዓ.ም በፊት ውይይት ሊደረግባቸውና ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ ያስገቡ ቢሆንም በዛሬው ስብሰባ በደብዳቤ ካሳወቋቸው ችግሮች ይልቅ የጊዜ ሰሌዳ ቅድሚያ የተሰጠው በመሆኑ የምርጫ ምህዳሩን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ብለው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫ ቦርድ የጠራውን ስብሰባ ረግጦ ወጣ




• ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ምህዳር እንዲኖር እንስራ የሚለው ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም
ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥቅምት 7/2007 ዓ.ም በ2007 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀውን 5ኛው አገራዊ ምርጫ በተመለከተ ከአገራዊ ፓርቲዎች ጋር ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ ረግጦ ወጣ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባውን ረግጦ የወጣው የምርጫ ቦርድ ምርጫው ፍትሃዊ እንዲሆን መስራት ያለበትን ነገሮች ሳይሰራና ፓርቲዎችም ያሉባቸውን ችግሮች አቅርበው መወያየት ሳይችሉ ስለ ጊዜ ሰሌዳ ማውራቱ አስፈላጊ አይደለም በሚል መሆኑን ስብሰባውን ለመሳተፍ ሄደው የነበሩት ተወካዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡



በስብሰባው ላይ የተገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ ስለ ጊዜ ሰሌዳው ከመወያየት በፊት ለምርጫ የሚያበቃ ምህዳር እንዲኖር በመስራት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቁ ሲሆን በ1997 ምርጫ ወቅት ፓርቲዎች ያሉባቸውን ችግሮች በዝርዝር መወያየታቸው ቢያንስ ቅድመ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ማገዙን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከ1997 ምርጫ በኋላ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች ችግራቸውን በዝርዝር በመወያየት፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ስለሚያስችሉ ጉዳዮች መነጋገር ባለመቻላቸውና ምርጫ ቦርድም በጉዳዩ በህገ መንግስቱና በአዋጁ የተሰጠውን ኃላፊነት ባለመወጣቱ የፖለቲካ ምህዳሩ እንደተዘጋም በመግለጽ ምርጫ ቦርድን ወቅሰዋል፡፡

ፓርቲዎቹ በ2005 የአዲስ አበባ፣ የድሬዳዋና የአካባቢ ማሟያ ምርጫዎች በፊት ምርጫ ቦርድ ኃላፊነቱን ሳይወጣ አዳማ ላይ ‹‹ስለ ጊዜ ሰሌዳው እንወያይ›› ብሎ ስብሰባ በጠራበት ወቅት ‹‹መጀመሪያ ለምርጫ የሚያበቃ ምህዳር እንዲኖር መወያየት አለብን›› ብለው ጥያቄ ቢያቀርቡም ቦርዱ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ከምርጫው ራሳቸውን ማግለላቸውን ገልጸው በዚህ አመትም ለምርጫ የሚያበቃ ምህዳር እንዲኖር እንደሚፈልጉ አሳስበዋል፡፡

Monday, October 6, 2014

የአዜብ ዱላ በሰሎሞን አስመላሽ ላይ…


ከአርአያ ተስፋማሪያም

ጋዜጠኛ ሰሎሞን አስመላሽ ለብዙዎች እንግዳ አይደለም። የ120 መዝናኛ አዘጋጅ ነበር። ከኢቲቪ ከወጣ በኋላ ሜጋ አመራ። (በ1989ዓ.ም ከሳምሶን ማሞ ጋር በታዋቂ አትሌት ላይ የሞከሩት የፔፕሲ ማስታወቂያ ማጭበርበር ድርጊት ነበር፤ ጉዳዩን ለጊዜው እንለፈው) የሜጋ ሃላፊዎች እግር ስር ወድቀው ከወጡ በኋላ ሰሎሞን አስመላሽ የራሱን ማስታወቂያ ድርጅት ከፍቶ መስራት ቀጠለ። በአደባባይ የገዢው ፓርቲ ደጋፊና አቀንቃኝ መሆኑን የሚናገረው ጋዜጠኛ ሰሎሞን ከአራት አመት በፊት በምሽት መዝናኛ ውስጥ መጠጥ እየተጐነጨ ነበር። በድንገት መብራት ድርግም ይላል።