Thursday, August 21, 2014

አብርሃ ደስታ ሃብታሙ አያሌዉና እና ኤርትራ

 ( ግርማ ካሳ)


ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራ ድርጅት ጋር እና ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በመገናኘት ፤ እንዲሁም ከባንክ በትዕዛዝ ብር በመቀበል የግንቦት 7 ተልዕኮና አላማ ለመፈፀም፤ ቁጥራቸው ከ60 በላይ የሆኑ ግለሰቦችን ለዚህ ጥፋት እንዲሰማሩ በማድረግ» የሚል ክስ ነው በወዲ ሃዉዜን/ትግራይ በሆነው አንጋፋ ፖለቲከኛ እና ብሎገር ላይ ክስ የቀረበው። ሌላው አንጋፋና አንደበተ ርትኡ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ፣ ሃብታሙ አያሌውም፣ «የግንቦት ሰባት ተባባሪ ነው» በሚል ነው ለመክሰስ ነው ዝግጅት እየተደረገ ያለው።


አብርሃ ደስታ እና ሃብታሙ አያሌው ፣ «ግንቦት ሰባትን ይደግፋሉ» የሚል ክስ ከቀረበባቸው፣ በተዘዋዋሪ መንገድ «ከሻእቢያ ጋር ወዳጆች ናቸው» ማለት ነው። ታዲያ የሻእቢያ ወዳጅ የሆነ ሰው፣ የኤርትራን መገንጠል ተቃዉሞ፣ ወይንም የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት መከበር እንዳለበት በማስመር ይናገራል ወይ ? እስቲ የጸረ-ሽብርና የአገር ደህንነት ተብዬው ምላሽ ይስጠን !!!
ሁላችንም እንደምናውቀው፣ በኤርትራ በኩል ትግል እናደርጋለን የሚሉ ወገኖች፣ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ሊናገሩ አይችሉም። በሻእቢያ ሥር እስካሉ ድረስ ቀይ መስመር ተሰምሮላቸዋል። እነ ግንቦት ሰባቶች፣ ኦነጎች ...፣ እርዳታ የሚያገኙጥ ከሻእቢያ ማእከላቼ ደግሞ አስመራ እስከሆነ ድረስ፣ «ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል» ብለው የመናገራቸው ነገር ጭራሽ የማይታሰብ ነው።

የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የዞን9 ጦማርያኑን እና የጋዜጠኞቹን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አደረገ (ዞን 9)

ስድስቱን የዞን ዘጠኝ አባላት ማለትም በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ፣ ማኅሌት ፋታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት እና አጥናፍ ብርሃነ እንዲሁም በሌለችበት ክሷ እየታየ ያለው በሶልያና ሽመልስ እንዲሁም በጋዜጠኞቹ ኤዶም ካሳዬ፣ ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ በልደታ 19ኛው የወንጀል ችሎት ዛሬ ጠዋት የተሰየመ ሲሆን ከሙስሊም ኮሚቴ አመራሮች ጋር በአንድ ችሎት እንዲታደሙ በመደረጉ የታሳሪዎችን ቤተሰቦችም ሆነ ወዳጆችን ለማስተናገድ ቦታ የለም በሚል ለጋዜጠኞች ብቻ የፍርድ ሂደቱ እንዲታይ በፖሊስ ተፈቅዶ ነበር፡፡

በሌለችበት የተከሰሰችው ሶልያና ሽመልስ መጥሪያ በጋዜጣ መውጣቱን ፍርድ ቤቱ ያረጋገጠ ሲሆን የዋስትና
መብትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ተሰይሞ የነበረው ችሎት በጸረ ሽብር አዋጁ መሰረት በአንቀጽ 3 የሽብር
ተግባራት ተብለው ከተዘረዘሩት ውስጥ አንድም ወይም ሁለትም ከዚያም በላይ ወንጀል የፈጸመ መሆኑ
ወይም ለመፈጸም ያቀደ ለመሆኑ ተገልጾ ክስ ሲቀርብ ነው በተመሰረተባቸው ክስ ዋስትናን ሊያሳጣቸው
የሚችለው ብለው ጠበቆቻቸው የተከራከሩ ሲሆን ደንበኞቻቸው በአዋጁ መሰረት የሰሩት የሽብር ተግባር ክስ
አልቀረበባቸውም ስለዚህ በአዋጁ ተጠቀሰ ማለት በአዋጁ መሰረት ክስ ቀርቧል ማለት ስለማይቻል
የዋስትናው ጥያቄ በመደበኛ ስርዓት እንጂ በጸረ­ሽብር ሕጉ መሰረት ሊታይ አይገባም፤ በተጨማሪም አዋጁ

ዋስትና ይከለክላል ተብሎ ቢተረጎምም ከሕገ­መንግስቱ ጋር ስለሚጋጭ ዋስትና ሊፈቀድላቸው ይገባል
ቢሉም፤ ፍርድ ቤቱ አንቀጽ ተጠቅሶ መከሰሳቸውን እንጂ በዚህ መከሰስ ነበረባቸው ወይም አልነበረባቸውም ብሎ ለማየት ፍርድ ቤቱ አይገደድም እንዲሁም የጸረ­ሽብር አዋጁ ከሕገ­መንግስቱ ጋር አይጋጭም ብለዋል በዚሁም መሰረት የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ተደርጎ ለጥቅምት 5 ቀን 2007ዓ.ም ቀጠሮ በመስጠት የዛሬው ችሎት የተጠናቀቀ ሲሆን ጠበቆቻቸውም የዋስትና ጉዳይ በተመለከተ ለጠቅላይ ፍረድ ቤት ይግባኝ እንደሚያቀርቡም ታውቋል፡፡

የወያኔ ጁንታ በግዳጅ እየሰጠ ባለው ስልጠና ከባድ ተቃውሞ ከሰልጣኞች እየገጠመው ነው ።

ምንሊክ ሳልሳዊ


የመንግስት ሰራተኛው እና የዩንቨርስቲው ተማሪዎች የከተቱት ስልጣና ላይ ወያኔ በጥያቄዎች ተወጥሯል፡፤

በሚቀርቡ የስልጠና ርእሶች ላይ ከፍተኛ አለመግባባት እና ጩኽት እየተከሰተ ነው፡፡


ከኑሮ ውድነቱ በባሰ ያቆሰሉን የሕወሓት አባላት ናቸው ።" የመንግስት ሰራተኛው


መልካም የልማት አስተዳደር በሚል ሽፋን ለመንግስት ሰራተኞች እና ለዩንቨርስቲ ተማሪዎች በተከታታይ ለ15 ቀን እየተሰጠ ያለው ስልጠና የወያኔን አመራሮች እና ከፍተኛ ካድሬዎች አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው መሆኑን እና ተቀባይነት ማግኘት እንዳልቻሉ ከሰልጣኞች የሚመጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።

ሰራተኞቹ እና ተማሪዎቹ በየፊናቸው ያነሱት ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ወቅታዊ ጥያቄዎች ወያኔዎች ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ከመነበቡም በላይ ለመመለስ ሲደናበሩ እና እፍረት ሲሰማቸው የታየ መሆኑን እና መጭውን እንደማይችሉት ስሜታቸው ላይ ሲነበብ እንደነበረ የጠቆመው መረጃ ከወያኔ ካድሪዎች አከባቢ የተገኘ መረጃ እንደጠቆመው ይህን ያህል አስጨናቂ ነገር ይነሳል የሚል ግምት ስላልነበረ ለአሰልጣኝ ካድሪዎች ቀድሞ የተሰጠው ስልጠና ምንም ውጤት ላይ ባለማሳየቱ አዳራሾች በተማሪዎቹ በፉጨት እና በከፍተኛ ተቃውሞ እንደተሞሉ መሆኑ ታውቋል።

Tuesday, August 19, 2014

የፀጥታ ሃይሎች በጭፍን ታዛዥነት የሚጥሷቸው መሰረታዊ መርሆች

ድምፃችን ይሰማ!

በሃገራችን ኢትዮጵያ ህገ መንግስት መግቢያ ላይ በግልፅ እንደሰፈረው ሃገራችንን እንዲመራ የሚመሰረተው መንግስት በኢትዮጵያ ህዝቦች ነፃ ፍላጎት፣ በህግ የበላይነት እና በህዝቦች ፈቃድ የህዝቡን የጋራ ጥቅም፣ መብት እና ነፃነት እንዲያስከብር የሚመሰረት የፖለቲካ ተቋም ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ተቋምም ህዝባችንን በትጋት እና በህግ በታቀፈ አካሄድ እንዲያገለግል ተደርጎ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባው ህገ መንግስቱ በጥብቅ ያሳስባል፡፡ በመቀጠልም ህገ መንግስቱ በአንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 ህዝቦች የሃገራችን ኢትዮጵያ ሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች መሆናቸውን ረጋግጣል፡፡ ከዚያም በመቀጠል በአንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 1 ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ማንኛውም የውስጥ ደንብም ይሁን መመሪያ ውድቅ መሆን ያለበት መሆኑን በማስገንዘብ ያሰፈረ ሲሆን በአንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 2 ደግሞ ማንኛውም የመንግስት አካልም ሆነ የፖለቲካ ድርጅት ለህገ መንግስቱ ተገዢ መሆን እንዳለበት በጥብቅ ያስገነዝባል፡፡

Wednesday, August 13, 2014

2007ን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሲባል እስከ ምርጫ ወይስ እስከ ዴሞክራሲያዊ መንግስት

ዳንኤል ተፈራ — የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ

በጣም በቅርቡ አንድ ስላልነገርኩት ስሙን የማልጠቅሰው ጉምቱ የሚባል ጋዜጠኛ ወዳጄና ሌላ አንድ ጎልማሳ ጋር ኢ-ወጋዊ በሆነ መንገድ ስለተቃዋሚ ጎራው ማውጋት ይዘናል፡፡ የጨዋታችን መነሻ ደግሞ አንድነትና መኢአድ ከብዙ ውጣ ውረድና ድርድር በኋላ ከፍፃሜ ለማድረስ ደፋ ቀና እያሉበት ያለው ውህደት ነው፡፡ የተቃውሞ ፖለቲካውን በቅርበት እንደሚከታተሉ አንዳንድ ግለሰቦች አስተያየት ‹‹ውህደቱ መሳካት አዎንታዊ ጎን ቢኖረውም ዘግይቷል፡፡ በዚህ ጊዜ የውህደቱ ጣጣ አልቆ፣ የሚተባበሩት ተባብረው ወደ ሰፊ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚገቡበት ነበር›› ይላሉ፡፡ የውህደቱ መሳካት ጥሩ ሆኖ ውህደቱም ሆነ ትብብሩ ዘለቄታ ላለው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት ወይስ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ? የሚል ጥያቄ አንስቶ መመለስ ተገቢ ነው፡፡

ጎልማሳው ሰው ቀበል አድርጎ ለተቃዋሚው ጎራ ቅርበት አለው ብሎ ስላመነ ይመስለኛል አይኖቹን እንደ ቆመህ ጠብቀኝ መሳሪያ ፊቴ ላይ ወድሮ ‹‹በተቃውሞ ጎራው በኩል ተቀራርቦ፣ ተባብሮና ተዋህዶ የመስራቱ ነገር እምብዛም ባለመለመዱ ወይም እስካሁን ባለመሳካቱ ይመስለኛል ውህደት እንዳንድ አደረጃጀትን የሚያጠነክር የፖለቲካ ስራ ሳይሆን እንደግብ ይታያል፡፡ ከፖለቲካ ጠቀሜታ አንፃር ሳይሆን ከምርጫ፣ ከግል ጥቅምና ዝና አንፃር ይታል፡፡ ውህደት እንዳንድ የለውጥ ማምጫ ስትራቴጅ ባለመታየቱ በህዝቡ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ነው፡፡ መጠላለፍና ሴራ በብርቱ የሚያጠቃው የፖለቲካ ባህላችን ግን ‹‹እኔ ብቻ አዋቂ፣ እኔ ብቻ ንጉስ›› ከሚል ጨፍላቂ ሰርዓት ጋር ሲደመር ግራ ማጋባቱ ላይገርም ይችላል፡፡

የምተችብህ ነገር አለ

ወያኔ ኢህአዴግ የኢትዮጲያን ታሪክ አበላሸ ፣ ሃገሪቱን እየበታተናት ነው፣ትውልዱን ወኔ ቢስ አረገው፣የትምህርት ፖሊሲው ትውልድ ገዳይ ነው ፣ ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች እየተጣሱ ነው ወዘተ ወዘተ ግን እኛ በግለሰብ ደረጃ ያለን አስተዋጽኦ ምን እንደሆነ የዘነጋን ይመስለኛል። ብዙዎቻችንም ስንጠየቅ የምንሰጠው መልስ እኔ አንድ ግለሰብ ነኝ ምን ላረግ እችላለሁ? እንዴ እንደ እኔ ለሃገሪቱ አሳቢና ተቆርቋሪ የት አለና ? እራሴን ማስጠቆር አልፈልግም ! ኦ ኦ የልጆች አባት ነኝ ልጆቼን ላሳድግበት ፣ ሃገር ቤት G+ ምንትስ የሆነ ቤት እየሰራሁ ነው ወይም ኢንቨስት እያረጉ ስለሆነ ቢነጥቁኝስ ወዘተ

ሀገር ቤት የበርበሬና የጤፍ ዋጋ ሽቅብ ወቶ ሰው ቁም ስቅሉን ሲያይ ዲያስፖራ ከሃገር ቤት እያስላካ ማኛ ጤፍ በቀይ ወጥ ካልበላሁ ሞቼ እገኛለሁ ይላል።ኢትዮጲያ ላይ በምግብ እጥረት ስንቱ እንደሚያልቅ ወይም የበሽታ ተጠቂ እንደሆነ እያወቅን ምግብ ተርፎት ይጥላል ።ደሞ ለምን ጠግባቹህ በላቹሁ ልትለን እንዳይሆን እንዳትሉኝ እስቲ አስቡት ተርፎን ከምንጥለው የምግብ መግዟ ላይ እኮ ጥቂት ሳንቲሞችን ባስቀምጥ እኮ ቢያንስ አንድ ወገኔን ከርሃብ ወይም ከበሽታ ለታደገው እችላለሁ ደግሞ እኮ እስቲ አስቡት እንዲህ ፈልጦት እንዲህ ቆርጦት ብይ ገዢውን ፓርቲ የምንተች እኛ የበቀለን ገረባ ልጅ በምን ይማር ፣ የአንዶለም ልጅ በምን ይኑር ለኛ ብለው ስቃይ የሚቀበሉትን የማላሳብ እኔ በምን ሞራል ኢህአዴግን እተቻለሁ።

Tuesday, August 12, 2014

ኢንጅነር ይልቃል የአውሮፓ ህብረት እርምጃ እንዲወስድ አሳሰቡ

ዛሬ ነሃሴ 6/2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተወካይ ያላቸው 20 የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ተወካዮች በተገኙበት አዲስ አበባ በሚገኘው የአውሮፓ ህብረት ቢሮ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ እንዲያስረዱ የተጋበዙት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ ወደባሰ ችግር ሳትገባ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚገባ አሳሰቡ፡፡

የአውሮፓ ሉዑካን ኃላፊ የሆኑት ሚስስ ባርባራ በመሩት ስብሰባ ላይ የተገኙት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በአሁኑ ወቅት ገዥው ፓርቲ ስለሚያደርገው አፈና፣ ሰብአዊ መብት ረገጣ፣ በሚዲያው ላይ ስለሚወሰደው እርምጃ፣ ስለታሰሩት ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞችና ጦማሪያን አስረድተዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ስለ ኢህአዴግ ሁኔታ በተጠየቁበት ወቅትም ‹‹ኢህአዴግ በራሱ ችግር፣ በርዕዮት ዓለም መደናበር፣ በአመራር ብቃት ማነስ ምክንያት ምርጫውን ክፍት በማድረግ ዴሞክራሲን መፍቀድ ዋጋ እንዲሚያስከፍለው ያውቃል፡፡ በሌላ ኩል ምርጫን ማጭበርበርም ጣጣ እንደሚያመጣበት ተረድቷል፡፡ በመሆኑም ምርጫ ማጭበርበርም ሆነ ምርጫውን ክፍት ማድረግ ችግር እንደሚፈጥርበት ስለሚያውቅ ከወዲሁ
አፈናን መርጧል›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የ”ብርቱው ሰው” መልዕክት – ከቃሊቲ እስር ቤት (በኤሊያስ ገብሩ)

‹‹ለእውነት መቆም ካልተቻለ ስብዕና ይወርዳል፣ ሕሊናህም ይሞታል››
‹‹የክስ እና የእስር መብዛት … የድል ጊዜ እየቀረበ መሆኑን ያሳያል››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ (ከቃሊቲ እስር ቤት)
‹‹እ… እስክንድር “The Iron man’’?››
የቃሊቲ ጠባቂ ፖሊስ

ጥቁር ሰኞ (Black Monday) ከሚሉት ወገን አይደለሁም፤ በአባባሉም አላምንም፡፡ እያንዳንዱ ግለሰብ በሁሉም ቀናቶች ጥሩም ሆነ ጥሩ ያልሆነ ሁነቶችን ሊያስተናግድ ይችላል፡፡ ይህንን ማለት የወድድኩት ዛሬ ሰኞ በመሆኑ ነው፡፡ ብዙዎች ዕለተ ሰኞ እንደሚከብዳቸው እና እንደሚጫጫናቸው ይናገራሉ፡፡ በቀናት መጥቆር እና መንጻት ማመናችንን ትተን፣ እያንዳንዱ ቀናቶችን ለሥራ እና ለመልካም ነገሮች በአግባቡ ብንጠቀምባቸው መልካም እያልኩ ወደዋናው ርዕሰ ጉዳዬ ላምራ፡-

18 ዓመት ተፈርዶበት በቃሊቲ ወህኒ ቤት ታስሮ የሚገኘውንና እጅግ የማከብረውን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን በቃሊቲ ከጠየኩት አንድ ወር ገደማ ሆኖኝ ነበር፡፡ ባለፈው ሳምንት ልጠይቄው አስቤ፣ በአዲስ የጋዜጣ ሥራ ተጠምቼ ስለነበር ሳልችል ቀረሁ፡፡ ዛሬ ግን፣ ከመኝታዬ እንደተነሳሁ የናፈቀኝን እስክንድርን ለመጠየቅ ወደቃሊቲ ማምራት እንዳብኝ ወሰንኩና ጉዞዬን ጀመርኩ፡፡

እውነት አብርሃ ደስታ አሸባሪ ነው? (ክብሮም ብርሃነ-መቐለ)

ነሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም የአረና ትግራይ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና የመቀሌ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር አብርሃ ደስታ በሽብር ተጠርጥሮ በተከሰሰበት ልክ በወሩ ፍ/ቤት እንደሚቀርብ በፌስ ቡክ አይቼ እኔም እንደ ዜጋና እንደ አድናቂው የሚቀርቡለትን የድራማ ክስ ለመስማት ጓጉቼ ፍ/ቤቱ ስደርስ እንደ እኔ አብርሃ ደስታን በአይናቸው ለማየትና የክሱን ድራማ ለማወቅ እንዲሁም ለቆራጡ ወጣት ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የሞራል ድጋፍ ለመስጠት የተሰባሰቡ የተለያዩ የክልላዊና ሀገራዊ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላት፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች እንዲሁም የወጣቱ ፖለቲከኛ አድናቂዎች ሽማግሌዎችና ወጣቶች ተደማምረው ያልገመትኩት የሕዝብ ብዛት በቡድን በቡድን ሰብሰብ ብለው የአብርሃ ቆራጥነትና የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ሲወያዩ አገኘኋቸው፡፡

ከኢህአዲግ/ወያኔ መላቀቅ ማለት ከድንቁርና ነፃ መውጣት ነው!

ሰሞኑን የኢህአዲግ/ወያኔ የኮምንኬሽን ሚኒስትር ዴታ የነበሩት አሁን በስደት የሚገኙት አቶ ኤርምያስ ለገሰ የሰጡትን መግለጫ  በኢሳት ቴሌቭዥን እየተከታተልኩ ነበር።አቶ ኤርምያስ ከተናገሩት ውስጥ የኢህአዲግ/ወያኔ አመራሮችም ሆኑ ቡድኑ ባጠቃላይ የተማሩ ኢትዮጵያውያንን ለምን እንደሚያሳድድ ያስረዱበት መንገድ ሚዛን የሚደፋ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።አቶ ኤርምያስ ኢህአዲግ/ወያኔ በመመርያው ውስጥ የተማሩ አባላት ከ 1% እንዳይበልጡ ለምን እንደሚደረግ እና ባጠቃላይ ድርጅቱ የተማሩ ኢትዮጵያውያንን የሚጠላበትን መሰረታዊ ምክንያት ሲያስረዱ እንዲህ ነበር ያሉት (ቃል በቃል ባይሆንም ሃሳቡን እንዲህ ይገለፃል) -

  ”ማየት ያለብን ድርጅቱን የሚመሩት ሰዎች አነሳስን ነው።እነኝህ ሰዎች ገና የ 16 እና 17 ዓመት ልጆች ሆነው ከግብርና ተነስተው (ግብርና የተከበረ ሙያ መሆኑን ሳንዘነጋ) ወደ ውግያ ገቡ።ዋናውን የወጣትነት ጊዜ ማለትም እውቀት የሚቀሰምበት እና የህዝቡን ማህበራውም ሆነ ቤተሰባዊ ሕይወት በማወቅያቸው ጊዜ ሁሉ ለአስራ ምናምን ዓመት የሚያውቁት መተኮስ ነው።አሸንፈው ቤተመንግስት ሲገቡ የመማርያ ጊዜ አልፏል።እኛ ያለፍንበትን የቤተሰብ ሕይወት እና ምክንያታዊነት ላይ የተመሰረተውን የዕውቀት መገብየት ዘመን አያውቁትም።ትምህርት ቤት አያውቁም፣ማህበራዊ ኑሮ አያውቁም።በመሆኑም  የተማረ ሰው አዲስ ሃሳብ ይዞ ከመጣ ይገለብጠናል ብለው ይሰጋሉ።” ነበር ያለው።ሚዛን የሚደፋ አገላለፅ ነው። 

የጸጋየ አየለ ገዳይ አሜሪካ ይገኛል

ደስታው አንዳርጌ (ዶ/ር)

ጸጋየ አየለ ይግዛው ይባላል። የ፴፬ ዐመት ባለትዳርና የልጆች አባት ነበር። ጎንደር ሆስፒታል ውስጥ በራዲዮሎጂስትነት ሲሰራ የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር አባል ነህ በሚል ፖሊስ የሚያደርስበትን ወከባ ለመሸሽ ወደ ደብረማርቆስ ሄዶ በአንድ የግል ክሊኒክ ተቀጥሮ መስራት ይጀምራል። ነገር ግን የፈራው አላጣውም ታህሳስ ፱ ቀን ፩፱፻፺፱ (1999) ዓ.ም ከጠዋቱ ፪ ሰዐት ከ ፵፭ አካባቢ ወደስራ ሲሄድ ፖሊስ ያለፍርድቤት ማዘዣ ይይዘዋል። ደብረማርቆስና ባህርዳር እያመላለሱ ለጥቂት ሳምንታት ካንገላቱት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተዛውሮ ታሰረ። ማዕከላዊ እንደደረሰ ለበርካታ ቀናት ከፍተኛ ድብደባና ማሰቃዬት ደርሶበታል። በደረሰበት ድብድባ እጅግ ሲደክም ራስ ደስታ ሆስፒታል ተወስዶ እንዲታከም ተደረገና ሲያገግም እንደገና ወደ ማዕከለዊ ተወስዶ ዘግናኝ ግፍ ተፈጸመበት። ጥፍሮቹ ተነቀሉ፤ የግራ ጆሮው፣ ሁለቱም እጆቹ፣ ብልቱ፣ አይኖቹ ሁሉ ከጥቅም ውጭ እስኪሆኑ ድረስ አሰቃዩት። እንዲህ አርገው ካሰቃዩት በኋላ በድብደባ ሽባ የሆኑትን እጆቹን በካቴታ ታስሮ ያድራል። ሲደክም እያሳከሙ ይደበድቡት ነበር። እንዲህያል ግፍም ይፈጸማል። ይህ ሁሉ አብረው ከሚሰቃዩት ታሳሪወችና ከቤተሰቦቹ ብቻ ሳይሆን ከጸጋየ ከራሱ ማረጋገጥ ተችሏል።

Monday, August 11, 2014

የከዱ የግንቦት 7 አባላት አቶ አንዳርጋቸውን እያሰቃዩ ነው ተባለ፤ * 2 መምህራንና 1 ዳኛ በአንዳርጋቸው ጉዳይ ታፍነዋል

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ ለወያኔዎች ከአዲስ አበባ እስከ ደብረዘይት ትልቁን የምርመራ ስራ እየሸፈኑ ያሉት ከግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሃይል ጋር በኤርትራ የነበሩ እና ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር የፖለቲካ ስራ ሲሰሩ የነበሩ በኋላም ከድተው የገቡ ቅጥረኞች መሆናቸው ታውቋል። እነዚህ ቅጥረኞች ከመጀመሪያው ሰርጎ ገቦች እንደሆኑ ሳይጠረጠር ወደ ግንቦት ሰባት ከገቡ በኋላ ከአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ቀደም ብሎ በመክዳት ወደ ወያኔ የተቀላቀሉ ናቸው ሲል ጦማሪ ምኒልክ ሳልሳዊ ዘገበ።

እንደ ምኒልክ ዘገባ ከሆነ በአዲስ አበባ እና በደብረዘይት ትልልቅ ሆቴሎች ተይዞላቸው በምርጥ መኪኖች እየተንሸራሸሩ አቶ አንዳርጋቸውን በማሰቃያ ክፍል ውስጥ በማምጣት እውነቱን አውጣ አንተ እንደዚህ ብለኸን አልነበረም በማለት በተለያየ ጊዜ በስብሰባ እና በውይይት ወቅት የተነጋገሩትን የፖለቲካ ኦፕሬሽኖችን እና የትግል ስትራቴጂዎችን በመጥቀስ ከፍተኛ ስቃይ እና ድብደባ እያደረሱብት ነው።

ለአንቺ ነው ኢትዮጵያ !

 ከእንግዳ ታደሰ


ከውሻ ተሻምቶ ለሚያድረው ህዝብሽ ነው ፣
ህዝብሽ እንዲጠግብ ሽቅብ ቁልቁል ያለው ፣ራሱን ረስቶ ህይወቱን የቸረው ፣
እድል እጣው ሆኖ በግፍ የታገተው፣
ለዚህ ነው ኢትዮጵያ ! ልጅሽ የታፈነው ፡፡
በማድያት የኳሉሽ – ፊትሽን ያጠለሹሽ፣
ዉብ መልክ ገጽሽን አመድ ያለበሱሽ ፣
በብተና ሴራ ከምድር ሊያጠፉሽ ፣
ታጥቀው ለተነሱት ቅጥረኛ ልጆችሽ ፣
በነው እንዲጠፉ ከመላዋ ምድርሽ ፣
ለዚህ ነው ኢትዮጵያ ! የባዘነው ልጅሽ ፡፡
ክራሞታችን እንዲህ ከሆነ – የወደዱትን አሳልፎ ፣
ምን ጠቀመ መማማሉ – አንገት ላንገት ተቃቅፎ ፡፡

‹‹አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ›› በበፍቃዱ ሃይሉ (ከቂሊጦ እስር ቤት)

[ከመቶ ሰባት ቀናት እስር በኋላ በፍቄ ሰለ እስሩ ስለ ምርመራው እና ስለ ወደፊት ተስፋቸው ከቂሊጦ እስር ቤት የሰደዳት መልዕክት ይቺትና። እኔ ጽሁፉን ሳነብ የመጣብኝ ሃሳብ እነዚህ ሰዎች በርካታ ንጹሃንን እስከዛሬ ማንም ሳያያቸው ሲያሰቃዩ የስቃዩ ሰለባዎች ዘጋቢዎች እና ጋዜጠኞች ካልሆኑ የስቃያቸውን መጠን የሚገልጹት በእንባ እና... ''ተወው... ተወው አይነሳ...'' በሚል ምሬት ብቻ ነበር። አሁን ግን በራሳቸው ጊዜ ዘጋቢዎችን ወደ ማዕከላዊ እያስገቡ እነሆ የኢህአዴግ ''አመራር ጥበብ''ን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ሰዕላዊ መግለጫ እየሰጡን ነው።
ኢህአዴግ ሆይ፤ በጥፊ በርግጫ አይገኝም ምርጫ፤ እያልን የበፍቄን ጽሁፍ ሁሉም ሰው ያነበው ዘንድ ይሄው...
‹‹አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ›› በበፍቃዱ ሃይሉ.
‹‹ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!››፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ፡፡ በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ‹‹አባሪዎቼ›› ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ የምርመራችንን ሒደት የሚገልፀው ጥያቄ፡፡ 

ዋ! ወንድሜን! (ጌታቸው አበራ)

ጌታቸው አበራ


ይድረስ ለወንድሜ “ለማላውቅህ”፣ ባረመኔ ገራፊዎች እጅ ለወደቅኸው፣
በኮረንቲ ሽቦ ገመድ – መላው አካላትህ ለሚላጠው፤
ከጭለማው የግፍ “ቻምበር” – ከሰቆቃ መፈጸሚያው፣
የስቃይህ ጣር ዋይታ – ላለም ጆሮ ለተሰማው።

ከህመምህ ስታገግም – ላንዲት ቅጽበት ብጠይቅህ፣
ምንስ ይሆን “ሃጢያትህ”? በነሱ ዐይን “ጥፋትህ”?
እኔማ ምን አውቄ?
ስቃይህን ሰምቼ እንጂ መጨነቄ፤

ግን፣ ግን…፣
ከሚያቃትተው ድምጽህ ዋይታ፣
እስኪ ልገምት …”መላ-ልምታ”፣
(በመዝገበ-ማሕደር ተከትቦ- ዓለም የሚያውቀውን እውነታ)፤
…ቆዳህን ባኮርባች ሲልጡ – ስጋህን በብረት ሲያቃጥሉ፣
አጥንትህን ፍቀው ሲግጡ – በስ ብልት ጠርሙስ ሲያንጠለጥሉ፣

Sunday, August 10, 2014

ትላንትና መኢአድ ያወጣው የትግል ጥሪ መግለጫ ወያኔን ብቻ ሳይሆን አሜሪካንንም አደናበሯል።

“መኢአድ ጠንካራ ድርጅት ነው።” በድንገት መኢአድ ቢሮ የደረሱ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች


 (ምንሊክ ሳልሳዊ)


በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ከኢሕአፓ ሕዋስ (ሴል) በመቀጠል በብቸኝነት ድርጅታዊ መዋቅሩን በማጥበቅ 
ታላቅ ስራዎችን የሰራው እና እየሰራ ያለው እንዲሁም በ97 ምርጫ የቅንጅት ማሸነፍ ታላቅ አስታውጾ 
የነበረው የፕሮፌሰር አስራት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በትላንትና እለት ለኢትዮጵያ 
ሕዝብ ባስተላለፈው የትግል ጥሪ የተደናገጡት ወያኔዎች ብቻ ሳይሆኑ የአሜሪካ መንግስት ዲፕሎማቶችም
 እንደሆኑ ከኤምባሲው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ethiopol

በትላንትናው እለት የመኢአድ እና የአንድነት አመራሮች በጋር በሰጡት መግለጫ መኢአድ ድርጅታዊ 
መዋቅሩን ተጠቅሞ የጎዳና ላይ አመጽ እንደሚጠራ እና ሕዝቡ በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ለምርጫ ቦርድ
እና ለወያኔም ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ይታወቃል። ይህ ያሰጋው ወያኔ እንደለመደው ሲራወጥ ሁኔታው
እና የመኢአድ ጥንካሬ ያሰጋቸው የአሜሪካ ዲፕሎማቶች በዛሬው እለት የፖለቲካ  ጉዳዮች ሃላፊ የሆነችዋ የኤምባሲው ዲፕሎማት በመኢአድ ጽ/ቤት በመገኘት አመራሮቹን ማነጋገሯ ታውቋል።

Friday, August 8, 2014

የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጡ መጠየቃቸውን ተቃወሙ


esatነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት የሰራዊቱ አባላት ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ተቃውሞ አሰምተዋል። በባድሜ አካባቢ የሰፈሩት የመከላከያ አባላት በደሞዝ ክፍያ ሳምንት መነሻው 200 ብር ሆኖ በየደረጃው ያሉ ወታደሮች እንደ ማእረጋቸውና ደሞዝ መጠናቸው እንዲከፍሉ ሲጠየቁ፣ የሰራዊቱ አባላት ደሞዛችን አይቆረጥም በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል።
ደሞዝ ከፋዮቹ ከላይ የመጣ መመሪያ ነው በሚል ሊያግባቡዋቸው ቢሞክሩም የሰራዊቱ አባላት ፈቃደኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል። አንድ የ3ኛ ሻለቃ አንደኛ ጋንታ አባል የሆነ ወታደር አመጹን መርተሃል ተብሎ ሊታሰር ሲል አምልጦ እስከነመሳሪያው ተከዜ ውስጥ ገብቶ መሞቱ ታውቋል። ይህንን ተከትሎ መጠናኛ ብጥብጥ መነሳቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰአት ውጥረቱ እንዳለ ሲሆን፣ ከመከላከያ እየጠፉ የሚሄዱትም ቁጥራቸው እየጨመረ ነው።

ታዋቂው ፖለቲከኛና ደራሲ ወጣት አብርሃ ደስታ ዛሬ ፍ/ቤት ቀርቦ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀበት!!

በአራዳ መጀመሪያ ፍ/ቤት ችሎት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይቀርባል ቢባልም ዘግይቶ 10 ሰዓት ከ25 ላይ ቀርቧል፡፡

ፖሊስ ሀምሌ 3 ቀን ፍ/ቤት ቀርቦ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ በሽፋን ትሰራለህ በሚል በቁጥጥር ስር አድርጎ ለምርመራ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት የነበረ ሲሆን በ28 ቀን ውስጥም ምንም ማስረጃ ለችሎቱ አላቀረበም፡፡


 በችሎቱ ላይ የአረና አመራር አቶ ካህሳይ፣የአብርሃ እህት በችሎቱ እንዲታደሙ ተፈቅዶላቸው ገብተዋል፡፡ አብርሃ ደስታ በእስርቤት የደረሰበትን ለችሎቱ ሲያስረዳ እያስገደዱ ቃል ተቀብለውኛል፣ ተደብድቤያለሁ፣ ከውጪ የመጡ የደህንነት ኃይሎች ምርመራ አድርገውብኛል፣ ጨለማ ቤት ለቀናቶች ነበርኩ፣ የማላውቀውንና ያላነበብኩትን እንደፈርም ተደርጌያለሁ፣ የጨጓራ በሽተኛ ሆኜ በግድ እንጀራ እንድበላ ተደርጌያለሁ በማለት ለፍ/ቤቱ አስረድቷል ፡፡ 

ፖሊስ እነዚህ ድርጊቶች በፖሊስ ጣቢያው እንደማይደረጉና ማስረጃ የሌላቸው ውንጀላዎች ናቸው በማለት ያስተባበለ ሲሆን፣ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ደንበኛቸውን የሚመረምረውን መርማሪ ስም እንዲገለጽ ቢጠይቁም የመርማሪውን ስም አንናገርም ይዞ ፍ/ቤት የሚያቀርበውን ፖሊስ ስም ብቻ ነው የምንናገረው በማለት መልሰዋል፡፡ 

አቃቤ ህግ ለምርመራ ተጨማሪ የ28 ቀን ቀጠሮ ጠይቆ ፍ/ቤቱ የ28 ቀን ቀጠሮውን ፈቅዶ ለነሐሴ 29 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት እንዲቀርብ አዟል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሂደት ለመከታተል አረና፣ የአንድነት፣ የሰማያዊ፣ የመድረክ፣የጌዴኦ የፓርቲ አመራሮችና አባሎቻቸው፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች በርካታ ሰዎች ተገኝተው አብርሃ ወደ ፍ/ቤት ግቢ በሚገባበትና በሚወጣበት ጊዜ በጭብጨባና አይዞህ በማለት አጋርነታቸውን ሲገልጹ ብርሃ ደስታም አንገቱን ዝቅ በማድረግ የታሰሩ እጆቹን ከፍ በማድረግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ፍኖተ ነጻነት

የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት7 የኦህዴድ ደግሞ ከኦነግ ጋር እያበሩ ነው ሲል አቶ አዲሱ ለገሰ ያዘጋጁትና ለጠ/ሚ አማካሪዎች የተላከው ሰነድ አመለከተ

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰነዱ ላይ ኢህአዴግ የአመራር ችግር እንዳጋጠመው፣ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ አለመሳካቱ እንዲሁም በጋምቤላ ተማኝ መሪ መጥፋቱ ተዝርዝሯል።
በሃምሌ ወር መጨረሻ የተዘጋጀው ሰነድ ግልባጭ ለጠ/ሚኒስትሩ አማካሪዎች ለአቶ በረከት ስምኦን፣ ለአቶ ደስታውና ለአቶ ኩማ ደመቅሳ ተደርጓል።

የቀድሞው ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ የፖሊሲ ስልጠና ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ ” የኢህአዴግን ተቃዋሚ ሃይላት ማንኮላሻ አቅም ግንባታ እና የአመራር ግንባታና የትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የፖሊሲ አማካሪዎች የቀረበ የሚለው ባለ 39 ገጽ ጽሁፍ፣ ኢህአዴግ ከላይ እስከታች የአመራር ችግር እንደገጠመው በዝርዝር ያቀርባል።

ዜና በጨዋታ፤ ሬድዋን ሁሴን በአሜሪካ ልብስ ስብሰባቸው ተስተጓጎለ

የመንግስት አፍ የሆኑት ሬድዋን ሁሴን ለራሳቸው በህግ አምላክ ብሎ የሚጮህ አንደብት እንኳ አጥተው ሂሳቸውንም ውግዘታቸውንም ችለው በዝምታ ዋጥ አድርገው ተስተውለዋል።

አሜሪካ ለስብሰባ የጠራቻቸው ባለስልጣኑ ልብስ ስብሰባ ገበያ ቢወጡም ኢትዮጵያ ውስጥ በሚሰሩት ነውር ተበሳጩ ኢትዮጵያውያን ከባልስልጣን መደዳ ብቻ ሳይሆን ከሰው ተራ አውጥተው ውጉዝ ከማሪዮስ ብለዋቸዋል።
በዚህም የተነሳ የባለስልጣኑ ልብስ ስብሰባ ተስተጓጉሏል።

Wednesday, August 6, 2014

መከሰሳቸውን ከፖሊስ ሳይሆን ከሚዲያ የሰሙት የሎሚ መጽሔትና የአፍሮታምይስ ጋዜጣ አዘጋጆች ይናገራሉ

“ስለመከሰሳችን የምናውቀው ነገር የለም”                                ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ 

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ
አቶ ግዛው ታዬ
የሎሚ መፅሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር
                        
ክሱን በተመለከተ የምናውቀው ነገር የለም። ከዚህ በፊት ከማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ይደወልልን ነበር። እዚያ ሄደን ቃላችንን እንሰጥ ነበር።
እኛ አሁን መገረም ነው የፈጠረብን። ሕገ-መንግስቱን አከበራለሁ የሚል መንግስት በምን መልኩ ነው የክስ ዝርዝር ሳይደርሰን፣ መጥሪያ እጃችን ላይ ሳይገባ በመገናኛ ብዙሃን ክሳችንን የሚያሰማን።

“ስለእኔ አታልቅሱ!”

 ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

“ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት፡፡ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ፡- እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን፡-
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

መካኖችና ያልወለዱ ማኀፀኖች፣ ያላጠቡ ጡቶችም ብፁአን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ፡፡” (የሉቃስ ወንጌል ም. 23 ቁ. 27-30) ከቅዱስ መጽሐፉ ይህን የመሲሁ የመጨረሻ ምክር የመረጥኩት (ምንም እንኳ ረቢው የተናገረው ስለመለኮታዊው ትምህርት ቢሆንም) ዓለማዊው ፍች የኢትዮጵያችንን የወቅቱን መንፈስ ለመረዳት ከማስቻሉም በዘለለ፤ በየጊዜው እያየን፣ እየሰማን ያለነውን የፖለቲካ ተቃውሞው የጥምዝምዞሽ መንገድ በአርምሞ ለመመርመር መልካም ምሳሌ ይሆናል በሚል እሳቤም ነው፡፡

የአርባ ምንጭ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎች ታሰሩ

ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዞኑ ፖሊሶች ትናንት ከሌሊቱ 10 ሰአት ላይ ወደ ሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አመራሮች መኖሪያ ቤት በመሄድ ፍተሻ ካደረጉ በሁዋላ ፣ አመራሮችን ወስደው አስረዋቸዋል።

የፍርድ ቤት ማዘዣ ይዘናል በማለት ፍተሻ ያካሄዱት ፖሊሶች በአንደኛው ቤት ውስጥ ሁለት ፍሬ ጥይቶችን ማግኘታቸውን ሲያስታወቁ፣ በሌሎች መኖሪያ ቤቶች ደግሞ
ቪዲዮ ካሜራዎችን፣ ፊልሞችንና የተለያዩ ወረቀቶችን ሰብስበው ወስደዋል። የአንደኛው አመራር የቅርብ ሰው የሆነ ለኢሳት ሲናገር፣ ፖሊሶቹ ጠመንጃ በሌለበት ሁለት
ጥይቶችን አገኘን ማለታቸው አስቂኝ ነው ካለ በሁዋላ፣ ሁለቱንም ጥይቶች ፖሊሶች ራሳቸው ይዘው መምጣታቸውንና አገኘን ብለው መናገራቸውን ገልጿል።

የዋሽንግተኑን የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያውያን ተቃወሙት

                                                 
                                                       "ኦባማ ዝምታው ይብቃ"
ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ የተከፈተውንና በዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ከአፍሪቃ መሪዎች ጋር የሚያደርጉትን ጉባኤ በመቃወም አደባባይ ወጥተዋል።

“በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብዓዊ መብት ረገጣ እንዲቆም አዎንታዊና ተጨባጭ ግፊት በማድረግ ፋንታ፤ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶቹን አራማጆች በመደገፍ ሁኔታው ይበልጥ እንዲባባስ እያደረገ ነው፤” ሲሉ ከተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች የመጡ መሆናቸውን ያስታወቁት የሰልፉ ተሳታፊዎች የኦባማን አስተዳደር ኮንነዋል።

ስብሰባውን አስመልክቶ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ርዕሰ-ብሔርነቱ በዘለቁ ወቅት ሃገራቸው ከነበረችበት የምጣኔ ኃብት ድቀት አሁን እያገገመች በመሆኗ ትኩረታቸውን ለአፍሪካ እየሰጡ መሆኑን የሚያሳዩ ክንዋኔዎችን እያደረጉ ነው በማለት ቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሣደር የነበሩትና የጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር ዴቪድ ሺን መናገራቸውን ያሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዘግቦ ነበር፡፡

Tuesday, August 5, 2014

የሕወሓት ጄኔራሎች ሲታመሱ ዋሉ ። በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን ነግሷል።

ምንሊክ ሳልሳዊ


በጥርጣሬ/ግምት ካልሆነ በቀር አስራ አራቱ መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም።
ሁለት ከፍተና የጦር መሃንዲስች ዱካቸው ደብረዘይት ከሚገኘው እስር ቤት ተገኝቷል።
ወደ መቀሌ ከዲያስፖራው ጋር ለዘረፋ የንግድ ሽርክና ኢንቨስተሮች ለመመልመል ያመሩት ጄኔራሎች ሳይቀሩ በምን እንደመጡ በማይታወቅበት ሁኔታ አዲስ አበባ ደርሰው የመሃል አገር መኮንኖች መጥፋትን ተከትሎ ያመጣውን ውጥረት በስብሰባ ሲያሹት እና ከተለያዩ ወታደራዊ ደህንነቶች መረጃ ሲሰበስቡ እንደዋሉ ታውቋል።

በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን የተፈጠረው ከምን የመነጨ ነው የሚል ጥናት በዚህ ሳምንት በተካሄደበት የመሃል አገር መከላከያ መምሪያዎች ውስጥ አጋጣሚ በተገኘ መረጃ 16 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም ሲል ሪፖርት ያቀረበው የወታ
ደራዊ ደህንነት ቡድን የቀረበለትን ጥቆማ ለበላይ አካላት ሪፖርት ሳያድርግ ፍተሻውን አጧጡፎት የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት 
ፍንጭ ባለማግኘቱ ትላንትና የተነገረው የበላይ አካል በከፍተኛ ድንጋጤ ተውጦ የዋለ መሆኑን ለጦር ክፍሎቹ ቅርብ የሆኑ ምንጮ
ቻችን ከመከላከያ ያደረሱን መረጃ ጠቁሟል።

ኢህአዴግ በድሆች ጉሮሮ ላይ ቁማር መጫወቱን ቀጥሎበታል፡፡ የደመወዝ ማሻሻያ ርካሽ የፓለቲካ ትርፍና ተግዳሮቱ

ምንሊክ ሳልሳዊ


***የደመወዝ ማሻሻያ ርካሽ የፓለቲካ ትርፍና ተግዳሮቱ….***
በድሆች ጉሮሮ ላይ ፓለቲካውን የሚያካብተው ኢህአዴግ በተቀጣሪዎቹ ላይ ቁማር መጫወቱን ቀጥሎበታል፡፡

ተቀጣሪው የኢትዮጵያ ህዝብም ባርነትን ወዶ መኖሩን ተያይዞታል፤ የሰውን ልጅ ከጫማህ ስር በባርነት ለማኖር ከፈለግክ ቤተሰብ መጦር ድሮ ቀረን እያዜመ በቤተሰብ የሚጦረው የዘመናችን የመንግስት ሠራተኛ አያድርሰው እንጅ ቢታመም ጉድ ፈላ! ያው ጤና አዳሙን፣ዳማከሲዩን፣ዝንጅብሉን አጥር ያፈራውን ሐረግ ሬሳ ይታጠናታል እንጅ እንኳንስ የግል ሆስፒታል በቀበሌው ያለ ጤና ጣቢያ ሔዶ በሐኪም ሊታይ አይችልም፤ በዓመት በዓል እንኳን ከመንግስት ሠራተኛ ቤት የልኳንዳ ፌስታል እንጅ የበግ ቆዳ የገባው በደጉ ዘመን ነበር፤ለመማር እራስን ለመለወጥ ገንዘብ ያስፈልጋል፤ከተማርክ ደግሞ ጥያቄ ማንሳትህ አይቀርም! የዛሬን ካልቸገረህ ስለ ነገህ ትሞግታለህ! ማኩረፊያ ካለህ ምሰህን አስከብረህ ለእራትህም ትተርፋለህ! ቅሉ ግን ከምሳ ባሻገር እንድትኖር አይፈለግም፡፡ ከምሳ ያለፈ እንድታስብ አይፈለግም! ሆድህ ከሞላ ቁንጣንህ ወንበር ያሰይሃል ተብሎ ይታመናል-በኢህአህዴግ ቤት! እራትህን እርግጠኛ ከሆንክ መታረዝህ ያሳስብሃል! ቁርሳቸውን ላላሟሹቱ ማሰብ ትጀምራለህ! ሌሎች መብቶችህም ትውስ ይሉህ ይሆናል! ከራስህ አልፈህ አገሬ ብለህም ትነሳ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ሆድህ ይሞላ ዘንዳ አይፈለግም፡፡ ደንደስህ ከወፈረ ለማነቆ አይመችም! የኢትዮጵያ የተቀጣሪዎች የደመወዝ እስኬል ዝቅተኛ ነው ብለህ ማንሾካሾ አትችልም፤ አደሃሪ ጓደኛህ 
ይቺ አገር ከዚህ በላይ ደመወዝ ለመክፈል አቅሟ አይፈቅድም ብሎ በሐገርህ ፍቅርህ ስስ ጎንህ በኩል ዘልቆ ይሞግትና ዝም ያሰኝሃል!
 አዎ! ይኢ አገር የተትረፈረፈ ደመወዝ መክፈል ያቅታት ይሆናል፤ እነ እንቶኔ ከጓሯቸው እንደ ባህር ዛፍ የሚያበቅሉትን ህንጻ መስሪያ
 የሚያክል ደመወዝ አልተመኘህም! ከእርሀብና ከእርዛት፣ከጥማትና ድቆሳ የሚያላቅቅ ገንዘብ ግን ኢትዮጵያ መክፈል አይሳናትም፤
 ደግሞስ የመሬቷ ኢትዮጵያ ይፋ የምትሆነው ደመወዝ ላይ ብቻ ነው እንዴ? የኢትቪዋ ኢትዮጵያ የት ገባች?

Monday, August 4, 2014

አንድ መቶ ሰባ አምስት ኪሎ ወርቅ ከሃገር ሊወጣ ሲል ቢያዝም በሳሞራ የኑስ ትእዛዝ እንዲያልፍ ተደርጓል።


ምንሊክ ሳልሳዊ

  • 661
    Share
የጄኔራል ሳሞራ የኑስ እንደሆነ የሚጠረጠረው አንድ መቶ ሰባ አምስት ኪሎ ወርቅ ከአገር ሊወጣ ሲል ተይዞ የነበረ ቢሆንም በጄኔራሉ ትእዛዝ ከአገር እንዲወጣ መደረጉን የአየር መንገዱ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል። ይህ በሁለት ካርቶን ታሽጎ በበረራ ቁጥር 600 እና 612 ወደ ዱባይ ሊሻገር ሲል በቁጥጥር ስር የዋለው ወርቅ በጊዜው ባለንብረቱ ተፈልገው ባለመገኘታቸው እንዲቆይ ቢደረግም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ቦታው ድረስ አሽከሮቹን በመላክ እንዲለቀቅ እና እንዲያልፍ/እንዲጫን የተደረገ መሆኑ ታውቋል።

ይህ የሃገር ሃብት የሆነን ወርቅ የወያኔ ባለስልጣናት ካለምንም ገደብ በማሸሽ እና በመዝረፍ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፒያሳ አከባቢ በሚገኘው በአፍሪካ ወርቅ ቤት ሽፋን እንዳልካቸው እና ዳንኤል በሚባሉ ስሞች በሚሊዮን ዶላሮች የሚገመት የወርቅ መጠን ከአገር በማስወጣት እና እንዲሁም የውጪ ወርቆችን ካለምንም የቀረጥ ክፍያ ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ስራ ላይ መሰማራታቸው በተጨማሪም ሃገሪቷ የምታገኛቸው የውጪ ምንዛሬዎች በጥሬው እየታሸጉ ከሃገር እንደሚወጡ ታውቋል።

Friday, August 1, 2014

የህወሃት ሽብር መቆም አለበት!

ዛሬ በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለ አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ መንግስት በመተቸታቸው በግልጽ በመጻፋቸውና በአደባባይ በመናገራቸው ከዚህም አልፎ በጥርጣሬ በተለይም በብሄረሰብ ማንነታቸው እያሳደደ የሚያፍን የሚያሰቃይና የሚገል የሽብር ተቋም ካለ ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መሬት ላይ ሰላማዊ ዜጎችን ኢላማ ያደረገ የተቃውሞ ሃይል በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ከወያኔ ውጪ አንዳች ሃይል የለም።
አፋኙ የወያኔ ስርአት በተለየም የህዝቡን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ የሚቀማጠሉት የህወሃት መሪዎችና ሎሌዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ በሰሙ ቁጥር እንደሚሸበሩና እንቅልፍ አጥተው እንደሚያድሩ ይታወቃል። አፍነውና ዘርፈው ገለው የሚገዙት ህዝብ ግፍ በዛብኝ ብሎ በተናገረ ቁጥር የሚሸበሩት እነሱ ብቻ እንጂ ህዝቡ አይደለም።