Thursday, July 31, 2014

41 አለማቀፍ ድርጅቶች የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማርያን በአፋጣኝ እንዲፈቱ ጠየቁ

የጸረ ሽብርተኝነት ህጉ ይሻሻል ብለዋል

ከዚህ በፊት በሽብርተኝነት የተፈረደባቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል
41 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የፕሬስ ነጻነት አቀንቃኞች፣ አለማቀፍና ክልላዊ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማትና የሙያ ማህበራት መንግስት በቅርቡ የሽብርተኝነት ክስ የመሰረተባቸውን ጋዜጠኞችና የዞን 9 ጦማርያን በአፋጣኝ እንዲፈታ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ከትናንት በስቲያ በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን ብሉምበርግ ኒውስ ዘገበ፡፡

ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ አርቲክል 19 ምስራቅ አፍሪካ፣ ሲቪል ራይትስ ዲፌንደርስ፣ ወርልድ አሊያንስ ፎር ሲቲዝን ፓርቲሲፔሽን፣ ፔን አሜሪካና የመሳሰሉት አለማቀፍ ድርጅቶች በጋራ በጻፉት ደብዳቤ፣ መንግስት ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን በሽብርተኝነት እየከሰሰ ለእስር መዳረጉን መቀጠሉ ያሳስበናል፣ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተገቢነት የሌለው በመሆኑ መገታት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

ሶስቱ ጋዜጠኞችና ስድስቱ ጦማርያን ሶስት ወራት ለሚሆን ጊዜ ይህ ነው የሚባል ክስ ሳይመሰረትባቸው ያለአግባብ በእስር ላይ መቆየታቸውንና አንዳንዶቹም በምርመራ ወቅት እንግልት እንደደረሰባቸው መናገራቸውን የጠቀሰው ደብዳቤው፣ ይህም አግባብ አለመሆኑን ገልጿል፡፡

Wednesday, July 30, 2014

የግል ሚዲያው “በፀረ ሽብር ህግ” ሊበላ ይሆን?

 [ኣቶ ግርማ ሠይፉ ማሩ]

የመንግሰትን ቀጣይ እርምጃ የሚያሳዩ ተከታታይነት ያላቸው በግል ሚዲያዎች ላይ የሚደረጉ ዘመቻው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ መልክቶች እየታዩ ነው፡፡ በቀጣይ ለሚቀርበው ዶክመንተሪ ተጋባዥ አንግዳ ሆኜ ለቆርጦ ቀጥሉ ኢቲቪ ቃለ ምልልስ እንደሰጣቸው ጥያቄዎቹ ደረስውኝ ተመልክቸዋለሁ፡፡ 

የጥያቄዎቹን ዝርዝር እንተወው እና ዓላማው ግን ባለፈው ከቀረበው ዘጋቢ ፊልም የተለየ ነገር የለውም፡፡ በነገራችን ላይ ባለፈው የቀረበውም ዘጋቢ ፊልም ላይ እንድሳተፍ ተጠይቄ እንደማይሆን ገልጨላቸው ነበር፡፡ ውሳኔዬ ትክክል መሆኑን ዘጋቢ ፊልሙን ካየሁ በኋላ ገብቶኛል፡፡ የዘጋቢ ፊልሞቹ ዋና ግብ “የኢህአዴግን አብዮታዊ ዲሞክራሲን መንገድ አምነው ያልገበሩ የግል የሚዲያ ተቋማትን ለማጥፋት ጥርጊያ መንገድ ማመቻቸት ነው፡፡”
የግል ሚዲያውን ማጥፊያ መንገዶች ሁሉን አቀፍ ናቸው፡፡ በዋነኝነት ኤኮኖሚያዊ የሚባለው ሲሆን ይህም በምንም ሁኔታ ከመንግስት ወይም “ከልማታዊ ባለሀብቶች” ገንዘብ እንዳያገኙ ማድረግ ሲሆን ከአንባቢ የሚሰበሰቡትንም ገንዝብ ለእዕትመቱ ቀጣይነት እንዳይመች የሚቻለውን ቀዳዳ ሁሉ መዝጋት፤ ይህ የማይሳካ ቢሆን በአሰተዳደራዊ ዘርፍ እንዲወሰድ የተቀመጠው ፍርድ ቤትን በመጠቀም ጋዜጠኞችን ማስር ነው፡፡

የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ክስ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ (አስቂኙ ክስና አስቂኙ ማስረጃ)

አገራችን ኢትዮጵያ በጥሩ ልትጠራባቸው የምትችላቸው ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው በድህነት በሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ በሙስና እና ሃሳብን ነጻነት በመግለጽ መብት የተለመዱ የምናፍርባቸው ጉዳዩች ሆነውመቀጠላቸው እሙን ነው፡፡ ሃሰብን በነጻነት መግለጽን አስመልክቶ ሶስት ወራትን ከፈጀ ምርመራ በኋላ በብዙ የፓሊስ ድብብቆሽሂደት የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ባለፈው አርብ ክስ መመስረቱም አብሮ ይታወሳል:

ጓደኞቻችን ከታሰሩ ጊዜ ጀምሮ መንግሰት ያቀረበውን ውንጀላ አስመልክቶ በተለያየ ወቅት ሃሳባችንን ለመግለጽ አስበን ምናልባትየምንሰጠው ሃሳብ አሁንም በመንግሰት እጅ የሚገኙት ጓደኞቻችን ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ በመፍራት እነዲሁም ለመንግሰትእድሉን በመስጠት ኦፌሻል ክሱን እስክናይ ድረስ በጠቅላላ ሃሳቦች ላይ አስተያየት ከመስጠት ውጨ ብዙም ሳንል ቆይተናል፡፡ አሁንግን ክሱ አንድ የዞን 9 ጦማሪን ጨምሮ በይፋ በመመስቱ እነዲሁም በክሱ ላይ ተጠቀሱት ክሶች አንዳቸውም እውነት ባለመሆናቸውክሱን አስመልክቶ ዘርዘር ያለ ማብራሪያ መስጠት እነዳለብን ተሰምቶናል፡፡

Tuesday, July 29, 2014

ስበር ዜና ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ህክምና ላይ የሚገኙት የአቶ በረከት ስሞኦን የጤነት ሁኔታ እያነጋገር ነው።


እሁድ ከአዲስ አበባ አንድ የጦር ሃይሎች ሆስፒታል ዶ/ር አስከትለው በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን እኩለለሊት ጅዳ ስውዲ አረቢያ ለህክምና በሚስጠር እደገቡ የሚነገርላቸው አቶ በረከት ስሞኦን በተለምዶ ብግሻን እይተባለ የሚጠራ አንድ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የልቡ ደም ቧንቧ ለማስፋት የተደረገላቸው መሆኑን ከሳውዲ አየር መንገድ ምንጮቻችን ለማረጋገጥ ተችሏል ። የመንግስት ባለስልጣኑ ጤንነት በአሁኑ ሰዓት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት እንዚህ ምንጮች ዛሬ ጠዋት ከመካ የዒድ አል ፈጠር የፀሎት ስረአት ባሃላ ሼክ አላሙዲን በስልክ እንዳነጋገሯቸው ይናገራሉ። አቶ በረከት ስመኦን ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ በድብቅ መምጣታቸውን የሚናገሩ እንዚህ የሳውዲ የአየር መገድ ምሲጥራዊ መረጃዎች ባለስልጣኑ በአሁኑ ሰዓት ጅዳ ሆስፒታል መተኛታቸው በተለያዩ የዜና ማስራጫዎች በመዛመቱ ህክምናቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ሳይጨርሱ ወደ ሃገር ሊመለሱ እንድሚቸል ገልጸዋል።

Monday, July 28, 2014

በስቃይ ላይ ተመርኩዘው የሚወጡ ቃላቶች የአንዳርጋቸው እንዳልሆኑ መናገር ይቻላል።

አባይ ሚዲያ፡ እንደተለመደው ሁሉ ወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብ እንደማያምናቸው በተረዱ ጊዜ በርካታ ዘዴዎችን እየፈጠሩ ማሀበረሰቡን እያዋረዱ ረግጠው ለመግዛት ያላቸውን ሃይል ሁሉ ተጠቅመው ለማሳመን ጥረት ማድረጋቸውን እያየን ነው። ይህም አንዳርጋቸው እኔ ደህና ነኝ በል ተብሎ ያለው እና “እንደምታዩት ነው” ያለው ትልቅ መልእክት አለው።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለሁለተኛ ጊዜ አወራ ያሉት ነገር ግን በየ 50 ሴኮንድና አንድ ደቂቃ ልዩነት በሆነ እየተቆራረጠ ኢዲት ተድርጎ መጀመሪያ አካበቢ የተቀረጸውን ምስል እንዲሁም የህዝቡን ቁጣ ለማብረድ የተጨመረበት መጨረሻው ደቂቃ ላይ ሌላ ልብስ ለብሶ የታየበት ምስል የወያኔን ጭንቀት የሚያጎላ እንጂ ከቶ የአቶ አንዳርጋቸው አንደበቶች  ሳይሆኑ መትረጌስና ሽጉጥ እንዲሁም ገዳይ ጅቦች ተደርድረው በማሰቃያ ቤት የተቀዳ ድምጽ እንጂ እንደሚሉት በፌድራል ምርመራ ጣቢያ አይደለም።

ሕወሓት አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ ራሷን በራሷ ያጋለጠችባቸው 4 ቅጥፈቶች

ስንታየሁ ከሚኒሶታ

እንደተጠበቀው በሕወሓት መንግስት በሚመራው የኢትዮጵያ ፖሊስ ፕሮግራም ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ተደርጓል። የአቶ አንዳርጋቸው በቲቪ መቅረብ ከዚህ ቀደም በአንዷለም አራጌ፣ በብርቱካን ሚደቅሳ፣ በደበበ እሸቱ፣ በአቡበከር አህመድ ላይ የተለመደ በመሆኑ ብዙም አስገራሚ አልሆነም። ሆኖም ግን ቪድዮውን ልብ ብሎ ለተመለከተው ወያኔ እንዳሰበው ትርፍ ሳይሆን የበለጠ ኪሳራ እንዳገኘበት ለመረዳት ችያለሁ። ለዚህም ነው ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ የረሳቻቸው 4 ቅጥፈቶች ስል ለዚህ አስተያየቴ ር ዕስ የሰጠሁት።

ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ ራሷን በራሷ ያጋለጠችባቸው 4 ቅጥፈቶች

1ኛ. ቪድዮው በጣም ኤዲት እንደተደረገ ያስታውቃል

ሕወሓት ያዘጋጀው የቪድዮ ካሜራ ማንና አቀናባሪው ደንጋጣ እንደሆነ ቪድዮው ያስታውቅበታል። በጣም ተቆራርጦ መቀጣጠሉ ከማስታወቁም በላይ ቢያንስ ከዚህ የተሻለ ኤዲቲንግ ሥራ መሥራት ይችል የነበረ ቢሆንም ይህን ባለማድረጉ ለፕሮፓጋንዳ ሥራ የተዘጋጀውን ቪድዮ ኪሳራ ላይ ጥሎታል። ቪድዮ አቀናባሪው ሆን ብሎ ሕዝብ መቆራረጡን እንዲያውቅ ያደረገ ከሆነ ልናደንቀው የሚገባ ሲሆን፤ ሆኖም ግን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ከሆነ ይህ ቪድዮ ቅንብሩ አይመጥንም።

ፖሊቲካና የግለሰብ ጠባይ

 (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም) 

ለእኔ ፖሊቲካና የግለሰብ ጠባይ እንደውሃና ዘይት የማይደባለቁ ነገሮች ይመስሉኛል፤ አጼ ምኒልክ ‹‹አመልህን በጉያህ›› ያሉት ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፤ ዘይትና ውሀ በባሕርያቸው የሚለዩትን ያህል ፖሊቲካና ግለሰብም የባሕርይ ልዩነት አላቸው ማለት ነው፤ የወያኔ መሪዎች ምንም ነገር የማይሰምርላቸው፣ ከመጀመሪያውኑ እነዚህን ሁለት የማይደባለቁ ባሕርዮች አደባልቀው በመንሣታቸው ነው፤ ፖሊቲካ ለማኅበረሰቡ መቆርቆር ነው፤ ለሕዝቡ መቆርቆር ነው፤ ለአገር መቆርቆር ነው፤ የፖሊቲካ መነሻም ይኸው መሆን አለበት፤ ዓላማውም የማኅበረሰቡ፣ የሕዝቡ ልማት እንጂ ጥፋት አይደለም፤ የነበረውንና ያለውን ማጥፋት የፖሊቲካ ዓላማ ሊሆን አይችልም።

የደርግ መንደር ምሥረታ የሕዝብ ዓላማ ነበረው፤ የዓላማው መሣሪያ ግን የሕዝብ ሳይሆን ወታደራዊ ጉልበት ነበር፤ በዚህም ምክንያት የሕዝብ ዓላማ ያለው ሥራ የሕዝብን ህልውና በሚፈታተን የጉልበት መንገድ መከተሉ ዓላማው እንዳይሳካ፣ ሕዝብና አገዛዙ ባላንጣዎች ሆኑ፤ ጥሩው ዓላማ በከሸፈ ጉልበተኛነት ሳይሳካ ቀረ፤ በመንደር ምሥረታው ዓላማ ደርግ ክፋት ወይም ቂም ቋጥሮ አልተነሣም፤ ስሕተቱ ከውትድርና ባሕርይ የመጣ ይመስለኛል፤

ማጥፋት ዓላማ ሲሆንና ጉልበት የማጥፋት መሣሪያ ሲሆን ፍጹም የተለየ ነው፤ማጥፋት የሚመጣው ከግል ጠብና
ከግል ቂም ነው፤ የራሱን ወይም የአባቱን፣ ወይም የእናቱን ቂም በልቡ ቋጥሮ ፖሊቲካ ውስጥ የሚገባ ሰው
ለጥፋት የተዘጋጀ ነው፤ ለጥፋት የተዘጋጀ ሰው ፖሊቲካ ውስጥ ሲገባ እሳት አደጋ መኪና ላይ ቆሞ ቤት
እንደሚያቃጥል ሰው ነው፤ አታላይ ነው፤ ዓላማውንም የዓላማውንም መሣሪያ አያውቅም፤ የሚንቀሳቀሰው
በጥላቻና በቂም ነው፤ ወይ የሕጻን ልጅ ወይም የተስፋ­ቢስ ደደብ ጠባይ ነው፤ እንዲህ ያለ ሰው ፖሊቲካ ውስጥ
የሚገባውም በዚሁ በደደብነቱ ምክንያት ነው፤ የደደቡ ፖሊቲከኛ ሥራ የማያስወቅሰው ፖሊቲከኛውን ብቻ
አይደለም፤ በዚያ ፖሊቲከኛ የሚመራው ሰው ሁሉ አብሮ የሚወቀስ ነው፤ እንዲያውም በፖሊቲከኛው እውቀትና
ችሎታ ማጣት የተነሣ የሚደርሰው ስቃዩና መከራው፣ ችግሩና አበሳው በዚህ ዓይነቱ ፖሊቲከኛ ላይ አይደርስም፤
ሰቃዩንና መከራውን፣ ችጋሩንና አበሳውን የሚጋፈጠው በዚህ ዓይነቱ ፖሊቲከኛ የሚመራው ሕዝብ ነው፤ ሕዝብ መሪውን በትክክል መምረጥ ያለበትም ለዚህ ነው፤ ተንጋሎ የተፋ ለራሱ ከፋ የሚባለው ይደርሳል።

ኦሮሞ እና እስልምና በ“ሕዳሴ አብዮት” መስመር

(ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

በወርሃ­ግንቦት ላይ ለዘመናት የተንሰራፋውን ሀገራዊ ደዌ ይፈውሳል ብዬ ተስፋ ስለማደርግበት “የሕዳሴ አብዮት” በሶስት ተከታታይ ክፍሎች ለመዳሰስ መሞከሬ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መጪው የ “ሕዳሴ አብዮታችን” መፍትሔ ሊሰጥባቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መሀል በዋነኝነት የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪው ማሕበረሰብ እና የእስልምና እምነት ተከታዮች የመብት ጥያቄን በተመለከተ በጥቅሉ ጠቃቅሼው አልፌ ነበር፡፡ ሆኖም ‘ሰፋ ብሎ ቢዳሰስ’ የሚሉ በተለያየ መንገድ የሚቀርቡ ጎትጓች ድምፆች መበራከታቸው የመነሻ ሃሳቡን ፈታ አድርጌ እንዳቀርብ አስገድዶኛል፤ እንግዲህ ይህ ጭብጥም የዛው ተከታይ መሆኑ ይሰመርልኝ፡፡


የኦሮሞ ጥያቄ

በኢትዮጵያችን ከሚገኙ በርካታ ብሔሮች መካከል አብላጫውን ቁጥር የሚይዘው ኦሮምኛ ተናጋሪው
ቢሆንም፣ ለዘመናት ይደርሱበት ከነበሩ ሥርዓታዊ በደሎች እና የባሕል ጭፍለቃዎች ዛሬም በምልአት ነፃ

እንዳልወጣ በቂ ማሳያዎች አሉ፡፡ በ1960ዎቹ አጋማሽ የአገሪቷ አደባባዮች የዘመኑን መንፈስ በተረዱ ቁጡ

ወጣቶች መጥለቅለቁን ተከትሎ፣ ‹በንጉሣዊው አገዛዝ ግብዓተ­መሬት ላይ የመጨረሻዋን ድንጋይ
ለማስቀመጥ› በሚል ሰበብ ቤተ­መንግስቱን መቆጣጠር የቻለው ወታደራዊው ደርግ፣ ህልቆ መሳፍርት
በሌለው መስዋዕትነት የተገኘውን ወርቃማ ዕድል ከጅማሮው አጨናፍጎታል፡፡ በግልባጩ አብዮቱን ካጋሙት ገፊ­ምክንያቶች ዋንኞቹ ለሆኑት የብሔርና የሕዝባዊ መንግስት ምስረታ ጥያቄዎች፣ መፍትሄ ይስጥ አይስጥ እስኪረጋገጥ ድረስ መታገስ ያልፈለገው ህወሓት፣ ጉዳዩ በደም መፋሰስ ብቻ እንደሚፈታ አውጆ ጫካ ሲገባ አዲሱ መንግስት ገና የ6 ወር ጨቅላ እንደነበረ አይዘነጋም፡፡  

Sunday, July 27, 2014

ተላላኪው ማን ነው? ታማኝ በየነ ጥያቄውን በማስረጃ ይተነትናል

ተላላኪው ማን ነው? ታማኝ በየነ ጥያቄውን በማስረጃ ይተነትናል።

     ታማኝ በየነ ከሲሳይ አጌባ ጋር ያደረገውን ውይይት ይመልከቱ:: 




Saturday, July 26, 2014

የተዓማኒነት ጉድለት ያለበት መንግስት…



መንግሰት የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ግራ ገብቶኋቸው ግራ የሚያጋቡን የመንግሰት ኃላፊዎች ያሉበት ሀገር ውስጥ ነው የምንገኘው፡፡ በሃላፊነታቸው ደረጃ የሚመጥን ማስተካከያ ለመውሰድ አቅምም ፍላጎትም የላቸውም፡፡ የተሸከሙት ሃላፊነት መንግሰት ብለው ለሚያስቡት አንድ ግዑዝ ነገር ለአገልጋይነት እንጂ፤ እነርሱ የመንግሰት አካል እንደሆኑ አይረዱትም፡፡ ይህን እንድንል የሚያደርገን መንግሰታችን ብለን በኩራት ግብር የምንከፍለው፤ መንግሰታችን ዜጎች በሰላም ወጥተው በሰላም አንዲገቡ የሚያደርግልን ተቋም ነው፤ ሀገራችን በልማት በልፅጋ ዜጎች የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ስርዓት ነው፣ ይህ ሁሉ ሆኖም ችግር ቢገጥመን በገለልተኝነት በፍትህ ስርዓት ዳኝነት የምናገኝበት ነው፤ ብለን ማመን ቢቸግረን ነው፡፡ እነዚህ የመንግሰት ሃላፊ ተብዬዎች እነርሱ የተጣለባቸውን ኃላፊነት መወጣት ሲያቅታቸው እኛ በእንድ ወይም በሌላ መንገድ ችግራቸውን በጠቆምናቸው ወደ ትክክለኛ ደረጃ ማደግ ትተው እኛ ወደ እነርሱ እንድንወርድ፣ እንድንዋረድ፣ ለሆዳችን እንድናድር ወደ ገደል ይጎትቱናል፡፡

የገነት ዘውዴ “ጠባሳ”

 (ከኢየሩሳሌም አረአያ)

እስክንድር አሰፋ ይባላል፤ አሜሪካ ለ22 አመት ከኖረ በኋላ አገር ቤት የገባው በዘመነ ኢህአዴግ ነበር። የት/ሚኒስትሯ ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ታናሽ ወንድም ነው። እስክንድር የቅርብ ወዳጄና ብዙ ነገር ያስተማረኝ ሰው ነው።..ሚያዚያ 1993ዓ.ም፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አድማ ይመታሉ። ወቅቱ ሕወሐት ለሁለት የተሰነጠቀበት ጊዜ ነበር። የትምህርት ሚ/ሯ ገነት ዘውዴ ለተማሪዎቹ ህጋዊና ሰላማዊ ጥያቄ በቲቪ የሰጡት ምላሽ የበለጠ ተማሪውን ቁጣ ውስጥ ከተተው።

እንዳውም ፈረንሳይ ለጋሲዮን ወደሚገኘው የገነት ወላጅ እናት መኖሪያ ቤት ተማሪዎቹ ይተማሉ። በሁኔታው የተደናገጠው እስክንድር ከግቢው ሾልኮ በመውጣት ወ/ሮ ገነት ወደሚኖሩበት የገርጂ ቤታቸው ያመራል። በጊዜው ገነት ከጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ታደሰ ጋር ተጋብተው ይኖሩ ነበር።..አመሻሽ ላይ አቶ ተፈራ ዋልዋና የወቅቱ የፖሊስ ኮሚሽነር ወርቅነህ ገበየሁ በወ/ሮ ገነት መኖሪያ ውስጥ ተገኝተዋል። 3ቱ በክብ ሶፋ ዙሪያ ተቀምጠው ይዶልታሉ።

Friday, July 25, 2014

ምንም ቢሆን ኢኮኖሚያችን በሁለት አሃዝ ማደጉ ይቀጥላል!!!

                                                                                                        ግርማ ሠይፉ ማሩ

“የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት” በያዘነው ሳምንት መጀመሪያ በህግ የተፈቀደለትን ሰማኒያ ከመቶ ጊዜ አጠናቆ ተዘግቷል፡፡ ስራውን እንጂ ግዜውን አላልኩም፡፡ በቀረው 20 ከመቶ በሚሆነው ጊዜ ባለፉት አራት ዓመታት ያከናወናቸውን ዓይነት ተመሳሳይ ተግባራት ያከናውናል ብሎመጠበቅ አይቻልም፡፡ ለዚህ ዋናውምክንያት ኢህአዴግ፣ በገዢነት 

በማንኛውም መንገድ ሊቀጥል እንደሚችል እርግጠኛ ቢሆንም፤ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት ግን መቀጠል አለመቀጠላቸውን የሚያረጋግጡበት ግልፅ የሆነ አሰራር ባለመኖሩ ስጋት ላይ እንደሚወድቁ ስለማውቅ ነው፡፡ ይህ ስጋት ካሁኑ መታየት ጀምሯል፡፡ ስለዚህ አብዛኞቹ የምክር ቤት አባላት፣ አሁን በቀጣይ ዕጣ-ፋንታቸው ላይ የሚወሰነውን የሚጠባበቁበት እና በግላቸውም ቢሆን አማራጭ የሚመለከቱበት ጊዜ ነው፡፡

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ደብረዘይት አየር ሃይል ግቢ ታስረው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው ነው


ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከሰኔ 18 ቀን 2006 ዓም ጀምሮ ደብረዘይት በሚገኘው የአየር ሃይል ግቢ ውስጥ
በአንድ አነስተኛ ክፍል ውስጥ ታስረው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ኢሳት የተለያዩ ምንጮችን አነጋግሮ ባሰባሰበው መረጃ አቶ አንዳርጋቸው በመጀመሪያዎቹ 10 ቀናት ከፍተኛ ድብደባ ከተፈጸመባቸው በሁዋላ ድበደባው ቆሞ፣ የማሰቃያ መርፌዎችን እየተወጉና
በኤልክትሪክ ሾክ እየተሰቃዩ መረጃ እንዲያወጡ እየተገደዱ ነው።

መርማሪዎች ከአቶ አንዳርጋቸው የሚፈልጉት መረጃ ከግንቦት7 ጋር በጋራ የሚሰሩ  አሁን በስልጣን ላይ ያሉ የኢህአዴግን አመራሮችን እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያሉ አዛዦችን ስሞች
ሲሆን፣ አቶ አንዳርጋቸው ግን እስካሁን ምንም አይነት መረጃ ባለመስጠታቸው ፣ መርማሪዎች ሲበሳጩ መታየታቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ለወትሮው አንድ መረጃ ሲያገኙ በታላቅ ደስታ
የሚፈነጩት መርማሪዎች፣ ምርመራቸውን ጨርሰው ሲወጡ የሚያሳዩት ብስጭት፣ እስካሁን ድረስ 

በውጭ ያለነው ኢትዮጵያዊያን ምርጫዎች አሉን! – አንዱ ዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ አርብ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፳፻፮ ዓመተ ምህረት

ዛሬም እንደሳምንቱ መብታችንን እያሉ ኢትዮጵያዊያን በየመስጊዱ ተሰብሰበዋል። በየቀኑ በየቤተክርስትያኑ ጸሎታቸውን ያደርሳሉ። በየትምህርት ቤቱ በራቸው ተንኳኩቶ እንዳይወሰዱ ተደብቀው ያጠናሉ። መምህራን በፍራቻ፤ ለተማሪዎቻቸው ሳይሆን ለካድሬዎቹ ይሽቆጠቆጣሉ። አርሶ አደሮች ለሚያርሱበት መሬት፣ ለማዳበሪያና ለካድሬ ሲሉ አንገታቸውን ደፍተዋል። ላብ አደሮች የሥራ ዋስትና አንገታቸውን አንቆ ወገባቸውን አጉብጦታል። ነጋዴዎች ከኤፈርት ጋር ውድድሩ ራቁታቸውን አስቀርቷቸዋል። ጋዜጠኞች ዓይኖቻችሁን ጨፍናችሁ እኔ የምላችሁን ካላደረጋችሁ ተብለው እስር ቤቱን ሞልተውታል። ማን ተርፎ? የፖለቲካ ምኅዳሩን ማነቆ የጨበጠው መንግሥት አምልኩኝ ብሏል። ሀገራችን ባለችበት የፖለቲካ ሀቅና እኛ አሁን ባለንበት ድንዘዛ፤ አንድ የሚያነቃ ብራቅ ብልጭ ሊልብን ይገባል። የአንድነት ውይይት የግድ ነው። ይቺ ሀገራችን ትልቅ ውጥረት ውስጥ ገብታለች። እኛም በያለንበት መሯሯጣችን አልቀረም። ነገር ግን በአንድ ላይ ሆነን፤ ምን መደረግ አለበት? የሚለውን ለመወያየት አልቻልንም። ለምን አንችልም? ታዲያ ምርጫችን ምንድን ነው? እኒህን ሁሉ እኮ ለመነጋገር መንገድ መፈለግ አለብን። እስከዛሬ ሌሎች ምን አደረጉ? ማለቱን ትተን፤ እያንዳንዳችን ምን 

አደረግን? ብለን ራሳችንን እንጠይቅ። ይህ ግን ለአንድነት መጠይቁ መንገድ እንዲከፍት አንጂ፤ እያንዳንዳችን ለየራሳችን የምንሠጠው መልስ አለን። ያ መልስ ያጠግባል? ወይንስ አያጠግብም? የየራሳችን መመዘኛዎች አሉን። ያ በቂ አይደለም። በስብስብ የአንድነት ጥያቄዎች ናቸው ወሳኞቹ። በአንድነት ወደ የት እየሄድን ነው? ወይስ የት ላይ ተገትረናል? ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን። የሚቀጥለው የኢትዮጵያ መንግሥት ምን መሆን አለበት? ያ ፍላጎታችን በምን መንገድ ይሳካል? ብለን አንድ ስምምነት ላይ መድረስ አለብን። በሀገር ውስጥ፤ የወገንተኛውን አምባገነን መንግሥት የግር ሠንሠለት እየፈተጉ፤ የሚቻላቸውን ያህል እየተራመዱ ነው። እኛስ አንጻራዊ ነፃነት ያለን፤ ምን ማድረግ አለብን? ጥያቄው ይህ ነው።

Thursday, July 24, 2014

ወይንሸት ፍርድ ቤት ቀረበች፣ አቤል ኤፍሬም ታሰረ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችን ማሰሩ እና ማዋከቡ ቀጥሏል

ኢየሩሳሌም ተስፋው (አዲስ አበባ)

ዛሬ የወይኒ ፍ/ቤት ቀጠሮ ስለሆነ በጠዋት የሰማያዊ ልጆች ከያለንበት ተሰባስበን ሜክሲኮ ወደሚገኘው እንደኛ ደረጃ ፍ/ቤት ሄድን ተሰባስበን ግቢ ውስጥ ቀመን ሳለ እነወይኒን የያዘው መኪና ሲመጣ ባለፈው ያየነውን ሽብር መንዛት ጀመሩ መብታችን አይደል እንዴ መከታተል እንዴት ከግቢ ታስወጡናላችሁ? አልን ከመሃላችን አቤል ኤፍሬምን ና ብለው ወደ ውስጥ አስገቡት እንዴ ለምን ትወስዱታላችሁ ስንል ቆይ አናግሬያቸው መጣሁ ብሎን ገባ የነወይኒ መኪናም ውደውስጥ ገብቶ መውረድ ጀመሩ ወይኒዬ ጭንቅላቷ እና እጇ እንደታሸገ ነው ፊቷ ላይ እሚነበበው ጥንካሬ አሁንም እንዳለ ቢሆንም አካሏ ግን እንደተጎዳ በደንብ ያስታውቃል ከፍተኛ ድብደባ እየደረሰባት እንደሆነ ትናንት ለነ ጌች ነግራቸዋለች እጥፍጥፍ ብላ አንገቷን ደፍታ ስትቀመጥ ሳያት የእውነት ከዚች አገር መፈጠራችንን ነው የጠላሁት ወይኒ እያየችን ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ መልኩ እንባዋ ይፈስ ጀመር ጭንቅላቷን እና እጇን እየነካች የስቃይ ፊት አሳየችኝ እሱንም ፖሊሶቹ እንዳይዋት በመሳቀቅ ነው በዚህ ሁሉ ስቃይ መሃል እጇን እየሳመች እንደምትወደን ደጋግማ ታሳየናለች።

ችሎት ገቡ ለሐምሌ 24 እንደተቀጠረ ከዛሬ ጀምሮ ሰው እንዲጠይቀት ፍ/ቤቱ እንዳዘዘ ነገረችን የነሱ መኪና ሲወጣ ወደ ቀጣዩ እስረኛ ጓዳችን ተጠግተን ለመጠየቅ ስንሞክር ሁከት ለመፍጠር ሙከራ አድርጓል ስለዚህ ሶስተኛ ወስደንዋል እዛ ሂዱና ጠይቁ አለን አንድ ጥጋብ አናቱ ላይ የወጣ ፖሊስ እኮ ወንጀሉ ምንድነው? ሁከት መፍጠር ምንም አይነት ሁከት አልፈጠረም መብቱን ነው የጠየቀው ያ ደግሞ ወንጀል ከሆነ ሁላችንም ወንጀለኞች ነን ሁላችንንም እሰሩን አቤል ምንም አይነት ወንጀል አልሰራም ብለን ሊቀ መንበራችን ኢ/ር ይልቃልን ጨምሮ ወደ 30 እምንሆን የሰማያዊ ልጆች ተሰብስበን ገባን።

መኢአድ የሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች መንግሥት በአስቸኳይ እና በተገቢው ሁኔታ መልስ እንዲሰጣቸው ጠየቀ

ከመላው ኢዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ

ለረዥም ጊዜ በሰላማዊና በሰለጠነ መንገድ ጥያቄዎቻቸውን ሲያቀርቡ በነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ህውሓት/ኢህአዴግ የወሰደውን የኃይል እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን ፡፡ እንደ መኢአድ እምነት ለጥያቄዎቻቸው ተገቢውን መልስ መስጠት ሲገባ በግልባጩ መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ ያሳዘነና ያስቆጣ የኃይል እርምጃ መወሰዱ የህውሓት/ኢህአዴግን ማንነት በተግባር ያሳየ ድርጊት ነው፡፡

ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም የእስልምና እምነት ተከታዮች በአንዋር መስጊድ በፀሎት ሥነ-ሥርዓታቸው ላይ ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲሰጣቸው በመጠየቃቸው ጥያቄዎቻቸውን ወደጐን በመተው የኃይል እርምጃ በመወሰዱ ችግሩ ይፈታል ብለን አናምንም፡፡ ሆኖም በእለቱ በእምነቱ ተከታዮች ላይ እና በአካባቢው በነበሩ ሰላማዊ ሰዎች ላይ የፀጥታ ሃይሎች የወሰድትን የሀይል እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ አሁንም ቢሆን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ጥያቄዎቻቸው በሰላማዊና ኢትዮጵያዊ ጨዋነት መፈታት አለበት ብለን እናምናለን፡፡ የህውሓት/ኢህአዴግ አባገነን ሥርዓት በእምነት ተቋማት ላይ እጁን አስረዝሞ የሚያደርገውን የአፈና ተግባር ማቆም አለበት፡፡

ግንቦት 7 ለብሔራዊ አንድነትና ነፃነት ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል ያስፈልጋል አለ

ግንቦት 7 በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያወጣው ር ዕሰ አንቀጽ እንደሚከተለው ተስተናግዷል።
በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙ የእብደት ተግባራትን ስናጤን ከፊት ለፊት ኢትዮጵያችንን እየጠበቀ ያለው መንታ መንገድ አመላካች ነው። ይህ ከፊት ለፊት የሚጠብቀን መንታ መንገድ አንዱ ወደ ብሔራዊ አንድነት፣ ነፃነትና ብልጽግና ሌላው ወደ እርስ በርስ ትርምስና ውድቀት የሚያመሩ ናቸው። የአንድነት፣ የነፃነትና የብልጽግና መንገድ ለመያዝ መስመራችንን ማስተካከል ያለብን ከአሁኑ ነው።
ለመሆኑ ከላይ ያልነውን ለማለት ያስቻሉን በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙት ተግባራት ምንድናቸው?
አንደኛ፤ ወያኔ፣ ዓለም ዓቀፍ ህግንና ሥርዓትን በጣሰ መንገድ ከየመን ባለሥልጣናት ጋር በማበር የንቅናቄዓችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማፈኑ በአለፉት ጥቂት ሣምንታት ውስጥ ውስጥ የተደረገ አብይ ክስተት ነው። ይህ የወያኔ የውንብድና ተግባር ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። ወያኔ፣ ለሀገር ነፃነትና ለእኩልነት የሚታገልን አንድ ታላቅ ሰውን ማፈንኑና ከእይታ ከልሎ እያሰቃየው መሆኑ በሕዝቡ ውስጥ ያለው ቁጣ ወደ መገንፈል አስጠግቶታል። አቶ አንዳርጋቸው በጠላት እጅ ከወደቀም በኋላ ኢትዮጵያዊያንን አሰባሳቢ ኃይል ሆኗል።
ሁለተኛ፤ ሰላምተኞቹን ብሎገሮችንና ጋዜጠኞችን በሽብርተኝነት በመክሰስ በቋፍ ላይ የነበረውን የወጣቶች ትዕግሥት እንዲሟጠጥ አድርጓል። ስለኢንተርኔት አጠቃቀምና ጥንቃቄ ሥልጠና መውሰድ በክስ ቻርጁ ውስጥ መካከቱ ሥርዓቱ ከእውቀት ጋር የተጣላ መሆኑ በግልጽ አሳይቷል። ከዚህም በተጨማሪ በህጋዊ ፓርቲዎች ውስጥ በንቃት የሚሳተፉ ወጣት መሪዎችን መርጦ በማሠርና በሽብርተኝነት በመወንጀል የወያኔ የአፈና መዋቅር ወጣቱ ላይ ማነጣጠሩ ግልጽ ሆኗል።

“አንዳርጋቸው ሽልማቱን መልሰህ ተቀበለኝ፤ አንበሳው የሚገባው ላንተ እንጂ ለኔ አይደለም” – ታማኝ በየነ (Video) | Zehabesha Amharic

“አንዳርጋቸው ሽልማቱን መልሰህ ተቀበለኝ፤ አንበሳው የሚገባው ላንተ እንጂ ለኔ አይደለም” – ታማኝ በየነ (Video) | Zehabesha Amharic

Wednesday, July 23, 2014

ኦሮሞ እና እስልምና በ“ሕዳሴ አብዮት” መስመር



(ተመስገን ደሳለኝ)

 በወርሃ-ግንቦት ላይ ለዘመናት የተንሰራፋውን ሀገራዊ ደዌ ይፈውሳል ብዬ ተስፋ ስለማደርግበትየሕዳሴ

አብዮትበሶስት ተከታታይ ክፍሎች ለመዳሰስ መሞከሬ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መጪው ሕዳሴ

አብዮታችንመፍትሔ ሊሰጥባቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መሀል በዋነኝነት የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪው ማሕበረሰብ

እና የእስልምና እምነት ተከታዮች የመብት ጥያቄን በተመለከተ በጥቅሉ ጠቃቅሼው አልፌ ነበር፡፡ ሆኖምሰፋ

ብሎ ቢዳሰስየሚሉ በተለያየ መንገድ የሚቀርቡ ጎትጓች ድምፆች መበራከታቸው የመነሻ ሃሳቡን ፈታ አድርጌ

እንዳቀርብ አስገድዶኛል፤ እንግዲህ ይህ ጭብጥም የዛው ተከታይ መሆኑ ይሰመርልኝ፡፡

 የኦሮሞ ጥያቄ

በኢትዮጵያችን ከሚገኙ በርካታ ብሔሮች መካከል አብላጫውን ቁጥር የሚይዘው ኦሮምኛ ተናጋሪው

ቢሆንም፣ ለዘመናት ይደርሱበት ከነበሩ ሥርዓታዊ በደሎች እና የባሕል ጭፍለቃዎች ዛሬም በምልአት ነፃ

እንዳልወጣ በቂ ማሳያዎች አሉ፡፡ 1960ዎቹ አጋማሽ የአገሪቷ አደባባዮች የዘመኑን መንፈስ በተረዱ ቁጡ

ወጣቶች መጥለቅለቁን ተከትሎ፣በንጉሣዊው አገዛዝ ግብዓተ-መሬት ላይ የመጨረሻዋን ድንጋይ ለማስቀመጥበሚል ሰበብ ቤተ-

ከኤርትራ ጋር የታቀደው ጦርነት ሊጀመር ነው!!!

ደመቀ የኔአየህ



የዛሬ ሦስት ወር አካባቢ የ ወያኔ መንግስት ከኤርትራ ጋር ጦርነት ሊከፍት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ከውስጥ የተላከልኝን መረጃ ማስነበቤ ይታወሳል።

የጦርነቱም ዋና አላማ በኤርትራ ውስጥ ያሉትን የነፃነት ታጋዮችን እንቅስቃሥሤ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማምከን የሚል ነው። 

የዚህ ጦርነት ዋና አላማ በስልጣን ላይ ያለውን የሻብያ መንግስት በመጣል በኢትዮጵያ ውስጥ ሲያዘጋጁቸው የኖሩትን የ ኤርትራ ተቃዋሚወች ወደ ስልጣን በማምጣት በኤርትራ ውስጥ ሊከሰት የሚችለውን 
ማንኛውም አይነት የትጥቅ ትግል ቦታ ማሳጣት ነው። 

ለዚህም ይረዳሉ ተብለው በ10ሺወች የሚሆኑ ኤርትራውያንን በኢትዮጵያ ዪኒቨርስቲወች 
ውሥጥ ሲያሥተምር ቆይቱል።

እነዚህ ተማሪወች ከአካዳሚክ ትምህርት ባሻገር በአመት  ሶሦት ጊዜ የ መንግስት አስተዳደር፣
የፓለቲካ እና የደህንነት ትምህርቶችን ሲማሩ ቆይተዋል።

ተስፋለም ወልደየስ፦ “ሚዛን” በሳተበት አገር “ሚዛን” ባለ ብዕሩን የተቀማ ጋዜጠኛ



 
አሁን በ እስር ላይ ከሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ተስፋለም ወልደየስ ነው። ዘሪሁን ተስፋዬ ስለተስፋለም ምስክርነቱን እንዲህ በማለት ይገልጸዋል።
(ከዘሪሁን ተስፋዬ)
ሌሊቱ ሊጋመስ ግማሽ ያህል ሰዓት ቀርቶታል። ወትሮም ዓርብ ምሽት ውክቢያ የማያጣው የአዲስ ነገር ቢሮ በግርግር ተሞልቷል። ጋዜጠኛ ወዲህ ወዲያ ይራወጣል። ቀሪው ኮምፒውተር ላይ አፍጥጦ ዘወትር ለሕትመት ዘግይቶ ለሚገባው ጋዜጣ ጽሑፉን ይተይባል። ጋዜጠኛ ተስፋለምም አንዲት ጥጉን ይዞ ይጫጭራል። ዜናዎች ኤዲት ያደርጋል። እኔም ለመጀመሪያ ጊዜ ይዤ የመጣሁትን ዜና ኤዲት እንዲያደረግ ሰጥቼው፤ ወደጀመርኩት የኢኮኖሚ ጽሑፍ ተመለስኩ። ነገር ግን አፍታም ሳይቆይ በንዴት እየቀዘፈ “አሁን በዚህ ሌሊት ይህ ዜና ተብሎ ይሠራል… ” ተስፋለም ይህን ይህል ግልጽ ነው። ለሞያው የሚቆረቆር። አንዳች ስህተት መስሎ የሚሰማውን ፊት ለፊት ከመናገር የማይቆጠብ።
ያን ሌሊት በብዙ ጭቅጭቅና ንትርክ ዜናው ተሰርቶ ወጣ። አጋጣሚው ግን ልዩነታችን በጋዜጠኝነት ፍልስፍና ላይ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር። እሱ “ሚዛናዊ” ብሎ የሚሟገትለት ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሥራዓት አንዳች የማያራምድ ይልቁንም ጋዜጠኝነትን አሽመድምዶ ልሳን የሚሸብብ መኾኑ ሊያግባባን አልቻለም። እኔ “balanced journalism is a zero-sum game in Ethiopia” ብዬ እሞግተዋለሁ፤ እሱ በየትኛውም የመንግሥት ሥራዓት ቢሆን የጋዜጠኝነት ሕግጋት የማይጣሱ ደንቦች ናቸው ይላል። ይህንንም በሥራው ያሳያል።
Tesfalem woldeyes
Tesfalem woldeyes
ጋዜጠኝነትን ሕይወቱ ያደረገው ተስፋለም፤ በምንም መልኩ ቢሆን ሞያው በትምህርት ቤት ያገኛቸውን የጋዜጠኝነት መርሖዎች እንዲቃረን አይፈልግም። ዜናዎች ሲያዘጋጅ “ሚዛናዊነት” የሚለው መርሕ አለመጣሱን ሲያረጋግጥ ብቻ ነው ወሬው የሕትመት ብርሃን የሚያየው። ይህ ግን በአንዳንድ ባልደረቦቻችን ላይ ጥርጣሬ አልጫረም ማለት አይቻልም። እሱ “ሚዛናዊ” ብሎ የሚጠራው ጋዜጠኝነት፣ ለዘብ የሚል በተለይም አንዳንድ ጠንካራ የሚባሉ ዜናዎችን (በአዲስ ነገር በወቅቱ ዕይታ) አግላይ ነው የሚል ክርክር ይስነሳ ነበር። የዜናዎቹ ‘ሚዛን’ ለመጠበቅ ሲባል ለዘብተኛ መኾናቸው “ተስፍሽ ለመንግሥት ተቆርቋሪነት ያሳያል” የሚል አንድምታ ያለው ጥርጣሬ ማሳደሩ አልቀረም።
ይሁንና በሚያዘጋጃቸው ዜናዎች ተዓማኒነት፣ ጥራት እና ቋንቋ አጠቃቃም ሁሉም የሚያደንቀው ነበር። በተለይ ማህበራዊ ገጾች ላይ የሚወጡ ጽሁፎችን እሱ ሳያይቸው እንዲወጡ የሚፈልግ ጋዜጠኛ አልነበረም። የመተረክ ችሎታው፤ የቋንቋ አጠቃቀሙ እና ዝርዝር ጉዳዮችን የማካተት ብቃቱ ልዩ ነው። ተግባቢነቱና ሁለ ገብነቱም የሞያ መርሕ ልዩነት ቢኖርም በሁሉም ዘንድ በፍቅር እንዲፈለግ አድርጎታል። የማይደክም ነው። የእንቅልፍ ሰዓቱ እጅግ በጣም አነስተኛ መሆኑ እንደ ሰው ቆሞ መሄዱ ሁሌም የሚገርመኝ ነው።

Tuesday, July 22, 2014

የትግል ጥሪ በውጭ ለመትኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ

የኢትዮጵያ ሕዝብ በወያኔ የአፈና ቀንበር ስር ከወደቀ አንስቶ በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በማህበራዊ ሕይወቱ እጅግ ወደከፋ አቅጣጫ እያመራ ይገኛል በተለይም የመንደር ፖለቲካው በኢትዮጵያዊያን መካከል ለመፍጠር እየተሞከረ ያለው ልዩነት ስርዓቱ እንዳሰበውና እንደሚፈልገው ገቢር አይሁን እንጂ አገዛዙ የለኮሰውን የጥፋት እሳት በአፋጣኝ ተረባርበን ካላጠፋነው ለወደፊት በኢትዮጵያዊነት ስሜት እና መንፈስ ላይ አደጋ የሚፈጥር ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር አምባገነኑንና ጎጠኛዉን የወያኔ አገዛዝ ለማስወገድ ከፍተኛ መስዋአትነት ከፍሏል። ድርጅታችን ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ጥቅም ሲል ዳገት ቁልቁለቱን፣ ረሃብና ጥሙን፣ ውርጭ ቸነፈሩን የኔ ብሎ በመቀበል አጥንቱን በመከስከስ ደሙን በማፍሰስና መተኪያ የሌላት ውድ ህይወቱን በመክፈል ለአገሩና ለሕዝቡ ያለዉን ጥልቅ ፍቅር በተግባር አስመስክሯል ።

በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለለውጥ ትግሉ በሰላማዊ ሰልፍ ፣ በሻማ ማብራት፣

Monday, July 21, 2014

በሰሜን ሸዋ የመርሃቤቴ ወረዳ ህዝብ ከወያኔ የፀጥታ ሃይሎችና ፌደራል ጋር ከባድ ውጊያ እያካሄደ ነው፣

ውጥረት በሰሜን ሸዋ መርሃቤቴ በርትቷል

ደብረብርሃን አከባቢ መግቢያና መውጪያ መንገዶች ተዘግተዋል።
ለወረዳው አለም ከተማና አካባቢዋ አገልግሎት ይውላል ተብሎ ከብዙ ጊዜ በሁአላ የገባውን መብራት የወያኔ መንግስት ህዝቡ የሚገለገልበትን መብራት አቁሞ ትራንስፎርሜሽኖቹን ነቅሎ ለአስቸኩአይ ጉዳይ ይፈለጋል ብሎ ወደ ትግራይ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የወረዳው 27ቱም ቀበሌ ተጠራርቶ ትራንፈርመሩን በቁጥጥር ስር በማድረግ ከላይ ከተጠቀሱት የወያኔ የፀጥታ ሃይሎች ጋር ኣሁን ድረስ ውጊኣ እያደረገ ሲሆን እስካሁን 7 የወያኔ ወታደሮች የሞቱ ሲሆን ከህዝብ ታጣቂ በኩል 1 ሞቷል። ባሁኑ ሰዓት ወረዳውን መሉ በሙሉ የህዝቡ ታጣቂ ተቆጣጥሮት ይገኛል። ወያኔ ከአዲስ አበባና ከተለያዩ አካባቢወች ተጨማሪ ሃይል ወደ አካባቢው እያንቀሳቀሰ መሆኑ ታውቁኣል።ሁኔታው የሚመለከታችሁ ወገኖች ሁሉ እየሆነ ያለውን ሁሉ በመከታተልና አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉ ያስፈልጋል።
ቁስለኞች ሆስፒታሉን አጣብውታል ። ቁስለኞቹ የሚታከሙት በፖሊስ ታጅበው ሲሆን ህክምናውን እንደጨረሱ ውእደ እስርቤት ይወሰዳሉ ።ከቦታው የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስከመቼ ተታለን እንኖራለን የሚሉ የሰሜን ሸዋ ነዋሪዎች ዱር ቤቴ ብለው ሸፍተዋል። ከዚህ በታች የምትመለከቱት ከአከባቤው ከሚገኘው ሆስፒታል የተላከልንን ምስል ነው።

ዶክተሮቹን በስልክ ለማነጋገር እንደሞከርኩት የወመኔው ወታደሮች ቁስለኞች ከቁጥር በላይ ናቸው።
23
10502071054430

ጅምላ ጨራሽ ተውሳክ (Biological Weapons) በድብቅ ወደ ትግራይ ተወሰደ


(ኢ.ኤም.ኤፍ) በመሰረቱ ጅምላ ጨራሽ ተውሳክ ወይም ባዮሎጂካል መርዝ በሰው ልጅ ላይ መጠቀም በተባበሩት መንግስታት የተከለከለ ነው። ሆኖም ይህንን የሰውን ልጅ በጅምላ የሚጨርስ ተውሳክ በህወሃት ጄነራሎች የሚመራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር በድብቅ ወደ አገር ውስጥ አስገብቶ ነበር። “ለምን እና በማን ላይ ግድያውን ለመፈጸም ነው?” የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ፤ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ክፍልም ቢሆን እንደዚህ አይነት ጥቆማ ቢደርሰው እርምጃ ለመውሰድ ይችላልና ኢትዮጵያውያን አክቲቪስቶችን ይህንን ጉዳይ ልብ ሊሉት ይገባል። እናም ዛሬ የደረሰን ዘገባ እንዳመለከተው ከሆነ፤የዛሬ ዓመት በድብቅ ተጭነው ወደ አገር ቤት ውስጥ የገቡትን አንትራክስ ስፓርስ (anthrax spores )፥ ብሩሲሎሲስ (brucellosis)፣ እና ቦቱሊስም (botulism) የሚባሉ ጅምላ ጨራሽ ባዮሎጂካል መርዞች ታሽገው ከተቀመጡበት ደብረዘይት መከላከያ ኮሌጅ ላቦራቶሪ ውስጥ ወደ መቀሌ ዛሬ ሌሊት በኮንቴነር ተጭነው እንደተወሰዱ ለማወቅ ተችሏል።
ጥቆማውን ያቀረበው እና አባ ኮስትር በሚል ስም መጠራት የመረጠው ግለሰብ ከሙያውም አንጻር ይህንን ጥቆማ መሰረት በማድረግ ለግንዛቤ እንዲሆን ከዚህ በታች ያለውን የግንዛቤ ጽሁፍ አዘጋጅቶ አቅርቧል።
biological_warfare
ሥነህይወታዊ በሽታ አምጭ(Biological Ethiologic Agents ) ተዉሳክን እንደ ጦር መሳርያ (Biological Weapons )የሰዉ ልጅ መጠቀም የጀመረዉ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 400 አ.አ የጦር ቀስትን በሞቱ እንስሳ ፈሳሽ ደምና የደም ተዋጾች መዘፍዘፍና ባላንጣን በመዉጋት ፤የኩሬ መጠጥ ዉሀን በመበከል እንደተጀመረ ከጤና ነክ መረጃወች መረዳት ይቻላል።የምራባዊያን ታሪካዊ ድርሳናትም ይህንኑ ያረጋግጣሉ።

በአብርሃ ደስታ ቤተሰብ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ከልክ አልፏል


(ኢ.ኤም.ኤፍ) ብዙዎች እንደሚያውቁት አብርሃ ደስታ በትግራይ የሚገኘው የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ነው። አረና ፓርቲ የህወሃት ተፎካካሪ ፓርቲ በመሆኑ፤ ወያኔዎች በአባላቱ ላይ ግፍ እና በደል ሲያደርሱ ቆይተዋል። አብርሃ ደስታም ትግራይ ሆኖ በዚያ የሚደረገውን ስር አት አልበኝነት በማጋለጡ፤ የትግራይን ህዝብ እንደካደ ተደርጎ ከድብደባ ጀምሮ የእስር እንግልት ደርሶበታል።  አሁንም ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ መኖሩ ይነገራል እንጂ፤ ህዝብ እንዲያየውም ሆነ እንዲጠይቀው አልተፈቀደም። ፍርድ ቤት ያቀረቡትም ሰውነቱ በጣም ደክሞ እና ተጎሳቅሉ ከእኩለ ለሊት በኋላ ነው።
Abraha Desta
አብርሃ ደስታ 

ይህ በአብርሃ ደስታ ላይ የሚደርሰው ስቃይ እና መከራ እንዳለ ሆኖ፤ እሱ ከታሰረ ጀምሮ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ ከፍ ያለ ግፍ እየተፈጸመ መሆኑን ከትግራይ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። እንዲህ ይነበባል።
• የአብርሀ ታናሽ እህትና የጤና ባለሙያ (የጤና መኮንን/ HO) የሆነችው ተኽለ ደስታ የኢህአዴግ አባልም ሁና የአብርሀ እህት ስለሆነች ብቻ ከስራ ተባራለች፣ ቢሮ እንዳትገባም በዘበኞች ተከልክላለች፣ መልቀቂያም ከልክለዋታል፤ ቀጣዩ ውሳኔም ቁጭ ብላ እንድትጠባበቅም ተነግሯታል፡፡
• ሁለቱ አዲስ ምሩቃን ወንድሞቹ ኣረጋዊ ደስታና ገ/ገርግስ ደስታ በከፍተኛ ብልጫ ሰቅለው የተመረቁ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው እነሱን ላለመቅጠርና ከነሱ ያነሰ ነጥብ ያላቸውን መቅጠሩ ተሰምቷል፤ አዋሳ ዩኒቨርሲቲም ተወዳድረው እንዳለፉ ሲነገራቸው ቆይቶ ሌሎች ከነሱ በታች የነበሩ ሲጠሩ እነሱ እስካሁን አልተጠሩም፡፡

ከድምፃችን ይሰማ የተላለፈ ጥሪ፦ “መንግስታዊው ‘ጥቁር ሽብር’ የህዝብን የድል ችቦ አያጠፋውም!”

ከቀናት በፊት በእለተ ጁምአ በታላቁ አንዋር መስጂድ በመንግስት ታጣቂዎች የተወሰደው ድንበር የለሽ ጭፍጨፋ የሙስሊሙ ህብረሰተብ ሰላማዊ ትግል በታሪኩ ሌላ መጠምዘዣ ውስጥ እንዲገባ ምክንያት እንዲሆን የሚያስገድድ ነው፡፡ በዚህ በመንግስት የደህንነት ኃይሎችና በፖሊስ ሀላፊዎች ከቀናት በፊት ታቅዶ በተወሰደ እርምጃ ከ6 ሺ በላይ የመንግስት ቅጥረኛ ሲቪል ለባሾች እንደተሳተፉበት መገለጹ ይታወሳል፡፡ ቅጥረኞቹ የተከበረው የረመዳን ወር የጁምአ ሰላት ከመሰገዱ በፊት በመስጊዱ ውጫዊ ሰሜናዊ አቅጣጫ ግርግር በማስነሳትና ከፖሊሶች ጋር ከሁለቱም አቅጣጫ ድንጋይ በመወራወር የታለመውን ውጤት ለማምጣት ሞክረዋል፡፡ በዚህም በአካባቢው የነበሩትን ጨምሮ በሁሉም አቅጣጫ የነበሩና በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች የጁምአ ሰላታቸውን እንዳይፈጽሙ እክል ከመሆናቸውም በላይ እጅግ በርካታ ጾመኛ ሙስሊሞች ላይ እጅግ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ፈጽመዋል፡፡
በእለቱ በተካሄደው ጭፍጨፋ እንደተለመደው የመንግስት የጦር ሜዳ ስልት ሙስሊሙን ከሁሉም አቅጣጫ በቆረጣ ስልት ለሰላት በተቀመጠበት በመቁረጥ በነፍስ ወከፍ በያዙዋቸው ዱላዎችና የመሣሪያ ሰደፎች ርህራሄ አልባ በሆነ ሁኔታ ደብድበውታል፤ ጭፍጨፋ አድርሰውበታል፡፡ ጭፍጨፋው እድሜ፣ ጾታ፣ አስተሳሰብና፣ የአካል ሁኔታን ሳያገናዝብ ነበር የተወሰደው፡፡

Sunday, July 20, 2014

“ ሽብርተኝነት የ21ኛው ክ/ዘመን የማደኛ መረብ በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቁራን እይታ::”

አንድ ለአምስት የወያኒቱ የስለላ ድር በዲያስፖራ



ይድረስ እንደ እኔ ከወገን ዘመዳችሁ ከሞቀ ቤታችሁና ከምትወዷት ሃገራችሁ ሳትወዱ በግድ እንጀራና ነጻነት ፈልጋችሁ ለተስደዳችሁ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼ፡፡ በኔና እንደ እኔ ከሁለት ያጣ ሆነን ጭንቀቴንና እየደረሰብን ያለውን ከፍተኛ ችግር ለናንተ ላዋያችሁ በውስጤ እንደ ሰደድ እሳት የሚቆጠቁጠኝን ችግሬን ላካፍላችሁ ወገኖቼን አስቸግሬ ወደ እናንተ እንዲያስተላልፉልኝ ቆርጬ ስነሳ አብረውኝ


በነበሩ ሌሎች ወገኖቼም ሆነ በራሴ ጉዳት እንዳይደርስ በመጨነቅ የማወጋችሁ አሳዛኝ እህታችሁ ነኝ፡፡ እኔ ሳላውቅ የገባሁበት ችግር ውስጥ ሌሎችም ብዙ ወገኖቼ ክብደቱንና መዘዙን ስይገባቸው የሃገራችን ጠላት የወያኔይቱ ተላላኪዎች እየተጠቀሙባቸው ስለሆነ ላስጠነቅቃቸው ፈልጌና የራሴንም ሃጢያት እግረመንገዴን ለመናዘዝ ናው፡፡

ምርጫ 97ትን ተከትሎ በወገኖቼና በቅርብ ዘመዴ ላይ በደረሰው ግድያ ምክንያትና ተደናግጬና ተስፋ ቆርጬ ትምህርቴን አቅዋርጬ የተሻለ ህይወትም ጭምር ፍለጋ ከሌሎች ጓደኞቼ ጋር ወደ አረብ ሃገር ተሰደድኩኝ፡፡ ብዙዎቻችሁ እንደሰማችሁትና አንዶአንዶቻችሁም ደርሶባችሁ እንደምታውቁት ዘግናኝ የስቃይና የባርነት ህይወት ለአራት አመታት ተሰቃይቼ በፈጣሪ ፈቃድ ወደ አውሮፓ ጠፍቼ ስደርስ በህይወት እንድንኖር ፈጣሪ የፈቀደልን ብቻ ነበርነ ለጊዜውም ቢሆን ሰላም ሃገር የደረስነው፡፡   

በዚህ የፈተና ጉዞ ከረሃቡና የበረሃው ጉዞ ስቃይ በተጨማሪ በማንም የግመል እረኛና የስደተኛን ንብረት በመዝረፍ የጠገቡ አመላላሽ ነጋዴዎች ንብረታችንን ብቻ ሳይሆን የነበረንን የሰውነታችንን ክብርና እየተፈራረቁ በወንድሞቻችን ፊት ብዙ አሳፋሪ ለመናገር እንኳን የሚሰቀጥጥ ግፍ ተፈጽሞብናል፡፡ ወንድሞቻችንም እንደኛው የያዙትን ንብረትና ጥሪት ተገፈው እየተደበደቡ ደክመው ህይወታቸው ያለፈና በየበረሃው ካለቀባሪ አሸዋ በልቶ ያስቀራቸው ባህር ላይ ለአሳ ነባሪ የገበርናቸው ጥቂት አልነበሩም፡፡

ሽብርተኝነት በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ '' ሁለተኛው ክፍል''




ሁሉን የሚያውቀውና የሚናገረው ታላቁ መጽሀፍ መጽሀፍ መጽሐፍ ቅዱስ ስለሽብር ምን ይለናል? መጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ሽብር በብዙ ቦታ ተጽፎ እናገኘዋለን ነገርግን ለዛሬ ስለሽብር የተወሰኑትን ከመጽሀፍ ቅዱስ ቃል ለእዚህ ጽሁፍ በማዘጋጀት እግዚያብሔር ሁከትና ሽብርን እንዴት እንደገለጸውና ትርፋቸውንና ጉዳታቸውን አብረን በእዚህ ጽሁፍ እናየዋለን::
“ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።” ማቴ 24:12
“ደግሞ ዲያቢሎስ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም አሳይቶ።ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው።ያን ጊዜ ኢየሱስ። ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው።” ማቴ 4: 8_10
“ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል።እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” ማቴ 5:43_45

የኢትዮጵያው ጓንታናሞ ቤይ ‹‹ ማዕከላዊ ››


maeklawi prison
ማዕከላዊ
አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳለፉት አመታት ሁሉ የኢትዮጵያን መንግስት የሚያስቆጣ ባለ 70 ገጽ ሪፖርት ከሁለት ሳምንታት በፊት ይፋ አድርጓል፡፡ የተቋሙን ሪፖርት ከሌላው ጊዜ የተለየ የሚያደርገው በአንድ ርዕሰ ጉዳይ በአንድ ተቋም  በማጠንጠኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የወንጀል ምርመራ ማዕከሎች መካከል በአዲስ አበባ ዕምብርት በሚገኘው ማዕከላዊ ተጠርጣሪዎች ግርፋት፣ማሰቃየትና ድብደባ እንደሚፈፀምባቸው ሪፖርቱ አትቷል፡፡
አሜሪካ በሁለቱ የኒውዮርክ መንትያ ህንጻዎቿ ላይ በአልቃይዳ የተቀነባበረ ጥቃት ከተሰነዘረባት በኋላ ‹‹ሽብርተኛ›› በማለት የሰየመችውን ቡድን አባላት ከምድረ ገጽ ለማጥፋት በጆርጅ ቡሽ ፊት አውራሪነት የሽብር ቡድኑ ዋነኛ መጠለያ ያለቻችትን አፍጋኒስታንን ወረረች፡፡ በዘመቻው በቁጥጥር ስር የዋሉ የአልቃይዳ አባላትና ተጠርጣሪዎች በጄኔቭ ስምምነት መሠረት በህግ የመዳኘት መብት እንዳያገኙ ለማድረግ የቡሽ አስተዳደር ከግዛቱ ውጪ በኩባ ድንበር የሚገኘውን ጓንታናሞ ቤይን ከዛሬ አስር አመታት በፊት ከጦር ካምፕነት ወደ ማሰቃያ ማዕከልነት አሸጋገረው፡፡
‹‹በሽብርተኝነት›› ተጠርጥረው ወደ ጓንታናሞ ቤይ እንዲገቡ የተደረጉ ተጠርጣሪዎች የዜግነት ስብጥር የሚበዛበት ቢሆንም አንዳንድ መረጃዎች የሚበዙት ተጠርጣሪዎች አፍጋናዊያን፣ ኢራቃዊያን፣ የመናዊያን፣ ሊቢያዊያንና ግብጻዊያን ስለመሆናቸው ይጠቁማሉ፡፡ ከታሳሪዎቹ መካከል 99 ከመቶ ያህሉም የሙስሊም እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡

ሰበር ዜና፣ የአሜሪካ ብሄራዊ የበረራ ባለስልጣን የአሜሪካ መንገደኞች አውሮፕላኖች በኢትዮጵያ የአየር ክልል እንዳይበሩ ጥብቅ ማሳሰብያ አስተላለፈ። ምክንያቱንም ሲገልጽ "የኢትዮጵያ መንግስት የመንገደኞችን አውሮፕላን ሊመታ ይችላል" ብሏል። የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲ.አይ.ኤ የወያኔ መንግስት የመንገደኞች አውሮፕላን መቶ በመጣል በተቃዋሚዎቹ ላይ ለማሳበብ ፍላጎት እንዳለው ሳይደርስበት አይቀርም።

FAA Prohibited Flight Operations in Ethiopian Airspace


Flight operations are prohibited in Ethiopian
(WP) – After Flight 17 was shot down in eastern Ukraine on July 17,                                                                                 the Federal Aviation Administration expanded an existing regulation                                                                           that prohibited certain flights from operating in the region. The FAA                                                                   regularly issues airspace restrictions and prohibitions for U.S.                                                                                   aircraft traveling through potentially hostile airspace.
Here’s where the FAA has issued flight advisories and prohibitions for U.S.                                                        aircraft as of July 18.
Ethiopia
Flight operations are prohibited in Ethiopian airspace north of 12 degrees                                                        latitude. The FAA also warns that Ethiopian forces may fire upon aircraft                                                               crossing into Ethiopian airspace from northeastern Kenya. View document »