Thursday, August 21, 2014

የወያኔ ጁንታ በግዳጅ እየሰጠ ባለው ስልጠና ከባድ ተቃውሞ ከሰልጣኞች እየገጠመው ነው ።

ምንሊክ ሳልሳዊ


የመንግስት ሰራተኛው እና የዩንቨርስቲው ተማሪዎች የከተቱት ስልጣና ላይ ወያኔ በጥያቄዎች ተወጥሯል፡፤

በሚቀርቡ የስልጠና ርእሶች ላይ ከፍተኛ አለመግባባት እና ጩኽት እየተከሰተ ነው፡፡


ከኑሮ ውድነቱ በባሰ ያቆሰሉን የሕወሓት አባላት ናቸው ።" የመንግስት ሰራተኛው


መልካም የልማት አስተዳደር በሚል ሽፋን ለመንግስት ሰራተኞች እና ለዩንቨርስቲ ተማሪዎች በተከታታይ ለ15 ቀን እየተሰጠ ያለው ስልጠና የወያኔን አመራሮች እና ከፍተኛ ካድሬዎች አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው መሆኑን እና ተቀባይነት ማግኘት እንዳልቻሉ ከሰልጣኞች የሚመጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።

ሰራተኞቹ እና ተማሪዎቹ በየፊናቸው ያነሱት ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ወቅታዊ ጥያቄዎች ወያኔዎች ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ከመነበቡም በላይ ለመመለስ ሲደናበሩ እና እፍረት ሲሰማቸው የታየ መሆኑን እና መጭውን እንደማይችሉት ስሜታቸው ላይ ሲነበብ እንደነበረ የጠቆመው መረጃ ከወያኔ ካድሪዎች አከባቢ የተገኘ መረጃ እንደጠቆመው ይህን ያህል አስጨናቂ ነገር ይነሳል የሚል ግምት ስላልነበረ ለአሰልጣኝ ካድሪዎች ቀድሞ የተሰጠው ስልጠና ምንም ውጤት ላይ ባለማሳየቱ አዳራሾች በተማሪዎቹ በፉጨት እና በከፍተኛ ተቃውሞ እንደተሞሉ መሆኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያን ታሪክ በተመለከተ በክፍተኛ ደረጃ ለማጣጣል ከመሞከር አንስቶ የቀድሞ መሪዎችን በመራገም ላይ ያተኮረው ስልጠና እንዲሁም በይበልጥ የአፄ ምንሊክን ታሪክ አፈር ለማስገባት የታቀደ እንደሆነ ተሰምቷል። የኢትዮጵያን ታሪክ ያለፉት 23 አመታት ብቻ ለማድረግ የታቀደውን ሂደት ያልደገፉት ተማሪዎቹም ይሁኑ ሰራተኞቹ ከፍተኛ ተቃውሞ በማሰማት አደራሾችን በጩሀት ሞልተውታል ። ከናንተ በተሻለ እኛ የአያት ቅድመአያቶቻችንን ታሪክ ስለምናውቅ እናንተ የምትነግሩን ታሪክ የፈጠራ እና የጥላቻ ነው ስለዚህ አናዳምጣችሁም የሚል መልእክት አስተላልፈዋል። የቀድሞ ባለታሪኮችን በማጣጣል ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንድትኖር ያደረጋት ኢሕአዴግ ነው የሚል አደምታ ያለው ስልጠና ተቀባይነት ሊያገኝ ባለመቻሉ በከፍተኛ ክርክር እና ጩሐት ውስጥ ያለፈ መሆኑን ተገልጿል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሰው ልጆች መብት እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ዙሪያ ከፍተና የሆነ አለመግባብቶች የተከሰቱ ሲሆን ካድሪውቹ መምእልስ አቅቷቸው ሲይስቀይሱ እና ሲያደናቡ ቢስተዋልም የወያኒ ለማደናበር መሞከር ፉጨት እና ጩኽትን እንዳስከተለ በየአደራሹ ስልጠናውን እየተከታተሉ ከሚገኙ ተማሪዎች የደረሰን መረጃ ሲያመለክት በየመንግስት ተቋማት ውስጥ ያለውን የበላይነት እና የሕዝብን መጉላላት በተመለክተ
ጥያቄ ያነሱት የመንግስት ሰራተኞች ስራችንን መስራት አልቻልንም ከኑሮ ውድነቱ በባሰ ያቆሰሉን የሕወሓት አባላት ናቸው ሲሉ አማረዋል። ደሞዝ ተጨመረ ሲባል ማንን ለማጭበርበር ነው ያሉት ሰራተኞቹ ጠብ ለማይል ነገር ከስራ ተባረራችሁ ቢባል ይሻለን ነበር ሲሉ ተናግረዋል። ዝግጅት ሳይደረግበት ለነጋዲዎች አቀባብላችሁ ሰጣችሁን ሌላ ኑሮ ውድነትን አመጣችሁብን እንጂ ምንም በደሞዝ ጭማሪው ያተረፍነው ነገር የለም። ሚዲያው የሚናገረው ከተጨመረው ጋር አይገናኝም ዝም እንዳላችሁ ዝም ብለን እየቆዘምን ብንኖር ይቻል ነበር ሲሉ ድምጻቸውን በስልጠናው ላይ አሰምተዋል፡፡

በተማሪዎቹ ዘንድ እየተሰጠ ባለው ስልጠና እጅግ ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ሕገመንግስቱ ለምን አልተተረጎመም ከወሬ ውጪ ህገመንግስቱን ኢህአዲግ እየጣሰው ነው፡፤ የሚከሰሱት ግን ህገመንግስቱ ይከበር ያሉ
ዜጎች ናቸው የሚል ጠንካራ ጥያቄ ጨምሮ የሽብር ትርጉም ይነገርን ሽብርተኛ ምንድነው አሸባሪውስ ማነው የሚሉ ትድጋጋሚ ጥያቂውች እና ከሃይማኖት ነጻነት አንጻር ያለውን እደምታ ልታስርዱን አልቻልችሁም አታደናብሩን የሃገሪቷ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ለምእራባውያን ብሄራዊ ጥቅም እና ለፖለቲካ አጀንዳ ሲባል ተዋርዷል፡ የሚሉ አስተያየቶችቸንአ ጥያቂዎች ተደምጠዋል። የሃገሪቱ ኢኮኖሚ አደገ ይባላል እንጂ ባለስልጣናት ቱጃር በሆኑበት እና በሙስና በትዘፈቁበት የአንድ ብሄር አባላት በድንገት በሃብት በተንበሸበሹበት ሁኔታ እንዴት ድህነት ተንሰራፋ ሲሉ ተማሪዎቹ አሰልጣኝ ካድሬዎቹን አፍጠዋቸዋል።

እጅግ የሚሰለች እና የሚያስጠላ ስልጠና ነው ይሉት ሰራተኞቹም ይሁኑ ተማሪዎቹ ምንም አይነት ፍላጎት አለማሳየታቸው እና ለጠየቁት ጥያቄ መልስ አለማግኘታቸው ከአሰልጣኞቹ ጋር ይመደብበርረና ስልጠናውን ጥለው እስከመውጣት የደረሱ መሆኑ ታውቋል። ስልጠናውን ጥለው ቢወጡም ከግቢ መውጣት እንደማይችሉ ተናግረዋል፤ለመጭው ምርጫ ድምጽ ለማሰባሰብ እየሮጠ የሚገኘው ወያኔ ድርጊቱ የሚያመለክተው በመፈረካከስ ላይ እንደሚገኝ እንዲሁም ሕዝቡ ፍርሃቱን እየለቀቀ የመብት እና የነጻነት ጥያቄዎችን እያነሳ መሆኑ አስደንግጧቸዋል።

የየቀኑን ስልጠናውን ውሎ በተመለከተ ማታ ማታ በከፍተኛ የወያኔ አመራሮች የሚመራ ስብሰባ የሚደረግ ሲሆን በተማሪዎቹ እና በሰራተኞቹ እየተሰጠ ያለውን አስተያየት እና ጥያቄዎች ዙሪያ የሚቀርብ ሪፖርት ለበላይ አካሎቻቸው እንደሚተላለፍ ታውቋል።

No comments:

Post a Comment