Monday, July 21, 2014

በሰሜን ሸዋ የመርሃቤቴ ወረዳ ህዝብ ከወያኔ የፀጥታ ሃይሎችና ፌደራል ጋር ከባድ ውጊያ እያካሄደ ነው፣

ውጥረት በሰሜን ሸዋ መርሃቤቴ በርትቷል

ደብረብርሃን አከባቢ መግቢያና መውጪያ መንገዶች ተዘግተዋል።
ለወረዳው አለም ከተማና አካባቢዋ አገልግሎት ይውላል ተብሎ ከብዙ ጊዜ በሁአላ የገባውን መብራት የወያኔ መንግስት ህዝቡ የሚገለገልበትን መብራት አቁሞ ትራንስፎርሜሽኖቹን ነቅሎ ለአስቸኩአይ ጉዳይ ይፈለጋል ብሎ ወደ ትግራይ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የወረዳው 27ቱም ቀበሌ ተጠራርቶ ትራንፈርመሩን በቁጥጥር ስር በማድረግ ከላይ ከተጠቀሱት የወያኔ የፀጥታ ሃይሎች ጋር ኣሁን ድረስ ውጊኣ እያደረገ ሲሆን እስካሁን 7 የወያኔ ወታደሮች የሞቱ ሲሆን ከህዝብ ታጣቂ በኩል 1 ሞቷል። ባሁኑ ሰዓት ወረዳውን መሉ በሙሉ የህዝቡ ታጣቂ ተቆጣጥሮት ይገኛል። ወያኔ ከአዲስ አበባና ከተለያዩ አካባቢወች ተጨማሪ ሃይል ወደ አካባቢው እያንቀሳቀሰ መሆኑ ታውቁኣል።ሁኔታው የሚመለከታችሁ ወገኖች ሁሉ እየሆነ ያለውን ሁሉ በመከታተልና አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉ ያስፈልጋል።
ቁስለኞች ሆስፒታሉን አጣብውታል ። ቁስለኞቹ የሚታከሙት በፖሊስ ታጅበው ሲሆን ህክምናውን እንደጨረሱ ውእደ እስርቤት ይወሰዳሉ ።ከቦታው የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስከመቼ ተታለን እንኖራለን የሚሉ የሰሜን ሸዋ ነዋሪዎች ዱር ቤቴ ብለው ሸፍተዋል። ከዚህ በታች የምትመለከቱት ከአከባቤው ከሚገኘው ሆስፒታል የተላከልንን ምስል ነው።

ዶክተሮቹን በስልክ ለማነጋገር እንደሞከርኩት የወመኔው ወታደሮች ቁስለኞች ከቁጥር በላይ ናቸው።
23
10502071054430

No comments:

Post a Comment