Thursday, July 17, 2014

በእነ ሀብታሙ አያሌው የክስ መዝገብ አንድነት ፓርቲ ያቀረበው ክስ ውድቅ ተደረገ


በዛሬው ዕለት በአራዳ ምድብ ፍታብሔር ችሎት ሀምሌ 8 ቀን 2006 ዓ.ም በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የፀረ ሽብር ዲቪዚዮን ኃላፊ ኮማንደር ተክላይ መብራህቱ የእስር ትዕዛዙንና የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀበትን ሰነድና ታሳሪዎቹን ይዘው እንዲቀርቡ ቢያዝም ኃላፊው ታሳሪዎቹን ሳይዙ ቀረቡ፡፡

ችሎቱ በ4፡30 ተሰይሞ ዳኛው ከሳሽና ተከሳሽ መቅረባቸውን ካረጋገጡ በኋላ እስረኞቹ መቅረባቸውን ዳኛው ጠየቁ፤ ተከሳሽ እስረኞቹን አለማቅረባቸውንና የሰነድ ማስረጃዎቹን ስላቀረብኩ እስረኞቹን እንዳቀርብ አይጠበቅብኝም በማለት ለፍ/ቤቱ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ዳኛው የእስር ማዘዣና የፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ሰነዶች ተከሳሽ ማቅረባቸውን ከገለጹ በኋላ ከሳሾች ያቀረቡት ክስ ውድቅ ሆኗል በማለትይህንን አቤቱታ ለማየት ስልጣን እንደሌለውና ለተከሰሱበት ችሎት አቤቱታችሁን ማቅረብ ነው ያለባችሁ በማለት ክሱ መዘጋቱን ገልጸዋል፡፡

ከአራዳ ፍረድ ቤት 6 የአንድነት አባላት ታፍነው ተወሰዱ
በዛሬው እለት በነሀብታሙ አያሌው የክስ መዝገብ አንድነት ፓርቲ ላቀረበው አቤቱታ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ለማድመጥ በችሎት ተገኝተው የነበሩ 6 የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት

1ኛ.ደንኤል ፈይሳ

2ኛ.አብነት ረጋሳ

3ኛ.ጥላዬ ታረቀኝ

4ኛ.ፋሲካ አዱኛ

5ኛ.ብርሀኑ ይግለጡ እና

6ኛ.መሰለ አድማሴ በደህነቶች ታፍነው በቶዮታ ደብል ጋቢና ኮድ 3-50559 መኪና ወደ ማዕከላዊ መወሰዳቸውን
የፍኖተ ነፃነት የማዕከላዊ ምንጮች ገልጸዋል።



No comments:

Post a Comment