Monday, July 21, 2014

ጅምላ ጨራሽ ተውሳክ (Biological Weapons) በድብቅ ወደ ትግራይ ተወሰደ


(ኢ.ኤም.ኤፍ) በመሰረቱ ጅምላ ጨራሽ ተውሳክ ወይም ባዮሎጂካል መርዝ በሰው ልጅ ላይ መጠቀም በተባበሩት መንግስታት የተከለከለ ነው። ሆኖም ይህንን የሰውን ልጅ በጅምላ የሚጨርስ ተውሳክ በህወሃት ጄነራሎች የሚመራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር በድብቅ ወደ አገር ውስጥ አስገብቶ ነበር። “ለምን እና በማን ላይ ግድያውን ለመፈጸም ነው?” የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ፤ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ክፍልም ቢሆን እንደዚህ አይነት ጥቆማ ቢደርሰው እርምጃ ለመውሰድ ይችላልና ኢትዮጵያውያን አክቲቪስቶችን ይህንን ጉዳይ ልብ ሊሉት ይገባል። እናም ዛሬ የደረሰን ዘገባ እንዳመለከተው ከሆነ፤የዛሬ ዓመት በድብቅ ተጭነው ወደ አገር ቤት ውስጥ የገቡትን አንትራክስ ስፓርስ (anthrax spores )፥ ብሩሲሎሲስ (brucellosis)፣ እና ቦቱሊስም (botulism) የሚባሉ ጅምላ ጨራሽ ባዮሎጂካል መርዞች ታሽገው ከተቀመጡበት ደብረዘይት መከላከያ ኮሌጅ ላቦራቶሪ ውስጥ ወደ መቀሌ ዛሬ ሌሊት በኮንቴነር ተጭነው እንደተወሰዱ ለማወቅ ተችሏል።
ጥቆማውን ያቀረበው እና አባ ኮስትር በሚል ስም መጠራት የመረጠው ግለሰብ ከሙያውም አንጻር ይህንን ጥቆማ መሰረት በማድረግ ለግንዛቤ እንዲሆን ከዚህ በታች ያለውን የግንዛቤ ጽሁፍ አዘጋጅቶ አቅርቧል።
biological_warfare
ሥነህይወታዊ በሽታ አምጭ(Biological Ethiologic Agents ) ተዉሳክን እንደ ጦር መሳርያ (Biological Weapons )የሰዉ ልጅ መጠቀም የጀመረዉ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 400 አ.አ የጦር ቀስትን በሞቱ እንስሳ ፈሳሽ ደምና የደም ተዋጾች መዘፍዘፍና ባላንጣን በመዉጋት ፤የኩሬ መጠጥ ዉሀን በመበከል እንደተጀመረ ከጤና ነክ መረጃወች መረዳት ይቻላል።የምራባዊያን ታሪካዊ ድርሳናትም ይህንኑ ያረጋግጣሉ።

የቅርቦችን ክንዉን ሰናስታዉስ በአንደኛዉ የአለም ጦርነት ጀርመን አንትራክስ (Anthrax)የተባለዉን በባክቴርያ በሶስት መንገዶች የሚዛመት ራሱን አካባቢዉ ሁኔታጋር በቀላሉ ሊቋቋም የሚችል(Spore former) እና በአፈር ላይ እስከ ፵ አመታት በላይ መቆየት የሚችል በተለይም ሳር የሚግጡ የቤት እንሰሳን የሚያጥቃ እና ከነሱ ጋር በሚደረግ ንክኪ ማለትም ቆዳቸዉ ሲነካ :-
1. በብነት መልክ በአየር(Aerosols )
2. ሰዉነታችን ላይ ቀላል ጭረት ካለ በንክኪ (Cutaneous) እንዲሁም
3. ሰጋቸዉንበመመገብ (Gastrointestinal) ወደ ሰወች የሚተላለፍ ሲሆን በተመሳሳይም ይህንኑ አንትራክስ በሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በጃፓን በሚስጥር በእስረኞች ላይ ተሞክሮ እስከ ሶስት ሺህ የሚሆኑ ሰወች ሰለባ ሆነወል።አሜሪካም ጀርመን በሁለተኛዉ የአለም ጦርነት ባዮሎጂካል መሳሪያን የምትጠቀም ከሆነ ምላሽ የሚሆናትን ለህክምናም ሆነ ለመከላከል አዳጋች የሆነዉን ለስጋ ዉጤቶች መመረዝ መንስኤ የሆነዉን ቦቱሊዝም የሚያመጣ (clostridium botulinum bacteria)የተሰኘ ባክቴሪያ ማዘጋጀትዋ ይታወሳል።በተጨማሪም ኤራቅ፤ ብሪታንያ፤ራሽያ ቬትናም የመሳሰሉ ሀገሮች የባዮሎጂካል ጦር መሳርያን የሚጠቀሙ ሲሆን በዉጤታማነቱም ሆነ በአቅርቦት ከኒውክሌር የተሻለና እጅግ ርካሽ መሆኑንም የተለያዩ የዘርፉ ምርምሮች ያመላክታሉ።
በዚህም መሰረት አንድ ግራም ባዮሎጂካል ቶክሲን (ቦቶሊዝም)አስር ሚሊዮን ያህል ሰዎችን በአንዴ ይገላል።ለምሳሌ ይሄዉ በላቦራቶሪ የተጣራ የቦቶሊዝም ቶክሲን የሰዉን ልጅ መተንፈሻ ና ነርቭ በማጥቃት ከሚታወቀዉ ሳሪን ኬሚካል ጦር መሳርያ(sarin chemical weapon ) ይልቅ ሶስት ሚሊዮን ጊዜ እጅግ ሲበዛ መርዛማ(potent) ነዉ።ቦቱሊዝም ሳሪን ኬሚካል ከሚሸፍነዉ የቆዳ ስፋት አንጻርም አንድ ግራም ቦቱሊዝም የሚባለዉን አደገኛ ገዳይ ቶክሲን አስራ ስድስት እጥፍ ማለትም ሶስት ሺህ ሰባት መቶ ያህል(3700) ስኩየር ካሬ ሜትር ቦታ ይሽፍናል።
ሌላ ጊዜ በሰፊዉ የምመለስበት ሆኖ ለጥፋት የተዘጋጀዉ አፍሪካዊ ናዚ ወያኔ እነዚህን በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ የተከለከሉ የባዮሎጂካል የጦር መሳሪያወች(Biological Weapons) አከማችቶ መገኘቱ እንደምታ ሊጤን ፤ ሊታወቅ ና መረጃዉ ተጣርቶ አለም አቅፍ ትኩርት ሊሰጠዉና ወንጀለኛዉ ትግራይ መራሹ የወንበዴ ቡድን እጅከፈጅ (Redhanded) ተይዘዉ ለፍርደ እንዲቀርቡ ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ።

No comments:

Post a Comment