Sunday, May 18, 2014

ሜይ 17ን ብመኘው?


ሜይ 17ን ብመኘው?

የኖርወይ ሕዝብ ሕገመንግሥታቸውን ያወጁት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1814 ማለትም የዛሬ 200 ዓመት ነበር።

አንድ መቶ አስራ ሁለት የአገሪቱ ታላላቅ ሰዎች በሀገር ፍቅር ቀናኢ ስሜት በመነሣሣት ሕገ መንግስቱን በዘመኑ ነባራዊ ሐቅ ላይ በመመሥረት እንዲሁም ጊዜ በፈቀደው ጥበብና ቋንቋ በአስደናቂ ክህሎት 
አረቀቁት ።
ታዲያ ይህ ሕገ መንግስት በወቅቱ የነበሩትን ባለስልጣናት የሚያገለግል ሳይሆን የሐገሪቱን ሕዝብን ማዕከል ያደረገና ከዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ዲሞክራሴያዊ ሕጎች ጋራ የተጣጣመ ረቂቅ ነበር ።

ይህ ሕገ መንግሥት በዚያን ጊዜ ተቀባይነትን አግኝቶ በከፍተኛ አድናቆት ቢፀድቅም ቅሉ፤እንደ ማንኛውም ሰው ሰራሽ ሕገመንግሥት ሁሉ፥ የሕዝቡን መሠረታዊ ጥያቄና ፍላጎት መሠረት በማድረግ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ የሆኑ መሻሻሎች ተደርገውበታል። 
ለዚህ እውነታ ዋቤ መጥቀስ ካስፈለገም በመጀመሪያው ረቂቅ ላይ እምብዛም ትኩረት ያልተሰጣቸው የሴቶችና የህፃናት መብት መከበርን የመሳሰሉት በጎላ ሁኔታ ተካተውበት ሕዝባዊነቱ የበለጠ ለዓለም ሁሉ ጎልቶ እንዲያንጸባርቅ ተደርጎአል። 
ታዲያ ይህ ሁሉ መሻሻልና ለውጥ የሆነው በሕዝብ ፈቃድ ብቻ እንጂ በማንም ግላዊ ውሳኔ አይደአለም።

Saturday, May 10, 2014

በግንቦት ወር የተከሰቱ 11 ታሪካዊ ሁነቶች


በግንቦት ወር የተከሰቱ 11 ታሪካዊ ሁነቶች


1. ግንቦት 1, 1947 ዓ.ም ሀገራቸውን ከድተው ለጣሊያን በባንዳነት ሲያገለግሉ የነበሩት የአስረስ ተሰማ የልጅ ልጅ የነበረው የቀድሞው አምባ­ገነኑ፣ ከፋፋዩና ጎጠኛው መሪ ለገሰ/ መለስ/ ዜናዊ የተወለደበት ቀን።

2. ግንቦት 8, 1981 ዓ.ም የሀገሪቱ ጄኔራሎች በመንግስቱ ሀይለማሪያም ላይ የመፍንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረጉበት ቀን።

3. ግንቦት 8, 1982 ዓ.ም በመንግስቱ ኃይለማሪያም ላይ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረጉት ጄኔራሎች የተረሽኑበት ቀን።

4. ግንቦት 13, 1983 ዓ.ም አምባ­ገነኑ፣ ሰው በላውና ጨፍጫፊው መንግስቱ ኃይለማሪያም ሀገሪቱን ጥሎ ወደ ዚምባቡዌ የፈረጠጠበት ቀን።

Wednesday, May 7, 2014

በእውቀቱ ስዩም ስለ ዞን 9 ጦማሪዎች፤ “የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም


በእውቀቱ ስዩም ስለ ዞን 9 ጦማሪዎች፤ “የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም”

ታዋቂው የስነጽሁፍ ሰውና ኮሜዲያን በእውቀቱ ስዩም በፌስቡክ ገጹ በእስር ላይ ስለሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያን የሚከተለውን አስፍሯል።

ነጻነትና ፍትህ በሌሉበት አገር ውስጥ የልማት አውታሮችን መገንባት የት ለመድረስ ነው?የባቡር ሀዲድ ግንባታ ሳይ ፣የሚመጣብኝ እንደ አይሁድ በባቡር ታጭቀው ወደ መግደያ ጣቢያ የሚጓጓዙ ዜጎችን ነው፡፡የኤሌክትሪክ ግንባታ ሳይ የሚመጣብኝ የኤሌክትሪክ መግደያ ወንበር ነው፡፡የሚቆፈር ነገር ሳይ ድቅን የሚልብኝ የጅምላ መቃብር ነው፡፡

Tuesday, May 6, 2014

የኃይለማርያም ደሳለኝ ቁልቁለቶች

የኃይለማርያም ደሳለኝ ቁልቁለቶች 


በ2005 ዓ.ም መጀመሪያ አቶ ኃይለማርያም “ጠቅላይ ሚኒስትር” ተደርጎ በኢህአዴግ ሲሾም፤ በፓርቲው ውስጥ አክራሪ ብሔርተኛ የአመራር አባላት ከመኖራቸው አኳያ፤ መቼም ቢሆን “ራሱን ችሎ ይቆማል” ብሎ መጠበቁ ተምኔት እንደሆነ በርካታ የፖለቲካ ተንታኞች መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ይህ ኃይል እንኳን እንደ ኃይለማርያም ላለ የድል አጥቢያ መሪ ቀርቶ፣ ከድርጅቱ ምስረታ ጀምሮ እስከ ምኒሊክ ቤተ- መንግስትም ድረስ ታላቅ የተጋድሎ ታሪክ ለነበረው አቶ መለስም ቢሆን ክፍተት ካገኘ አለመመለሱን የ93ቱ ሣልሳዊ ህንፍሽፍሽ በግልፅ አሳይቶ ማለፉ አይዘነጋም፡፡ በተጨማሪም ራሱ መለስ ዜናዊ በድህረ ምርጫ 97 የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ዘብጥያ ወርደው የነበሩትን የቅንጅት አመራሮች “ከእስር
እንዲፈቱ ብፈልግም አክራሪው ኃይል ተቃወመኝ” ማለቱን ዊክሊክስ የተሰኘው የመረጃ መረብ የአሜሪካ አምባሳደርን ጠቅሶ ይፋ ማድረጉ ይህንኑ ያስረግጣል፡፡ የአምባሳደሩ መረጃ የተጋነነ፤ አሊያም “ተጋግሮ የቀረበለት ነው” ሊባል ቢችል እንኳ “ጭስ በሌለበት...” እንዲሉ፤ በግንባሩ ውስጥ አክራሪ ኃይል ለመኖሩ በጠቋሚነት ሊወሰድ ይችላል፡፡

Friday, May 2, 2014

ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ምድር የዘራው የብሄር ፈንጂና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን!

ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ምድር የዘራው የብሄር ፈንጂና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን!

Abrha-Desta1-150x150
  • digg
  • 1496
    Share
በአዲሱ የአዲስ ማስተር ፕላን በአዲስ አበባ ዙርያ ያሉ የኦሮምያ ክልል ገጠር መሬቶች የአዲስ አበባ ከተማ አካል ያደርጋቸዋል። ይሄን ጉዳይ በኦሮሞ ህዝብ ባጠቃላይ በኦሮሞ ተማሪዎች ደግሞ በተለይ ዓመፅ አስነስቷል።
ማስተር ፕላኑ የገጠር ቦታዎች ማካተቱ በራሱ ችግር አይደለም። እንዳዉም ፕላኑ ኦሮምያ አልፎ መቐለም ቢያጠቃልል ደስ ባለኝ ነበር። ከተማ ቢያድግ መልካም ነው። ከተማ ሲያድግም በዙርያው ይሰፋል። ይህ ባህርያዊ ነው። ግን ችግር አለ። በኢህአዴግ ዘመን እየተስተዋለ ያለው የከተሞች ማስፋፋት ስትራተጂ አፈፃፀም ኗሪዎችን እጅግ ይጎዳል።

Thursday, May 1, 2014

በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ የኦሮሞ ብሔር ተማሪዎች ባነሷቸው ጥያቄዎችና እየደረሰባቸው ያለው ጉዳይ

በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ የኦሮሞ ብሔር ተማሪዎች ባነሷቸው ጥያቄዎችና እየደረሰባቸው ያለው ጉዳይ

በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል መካከል ይተገበራል የተባለውን ማስተር ፕላን ተከትሎ ተቃውሞ፣ ድጋፍና ገለልተኛ የሆነ አቋም እያየው ነው። መጀመሪያ ደረጃ ማንም ጤነኛ ሰው ልማትን አይጠላም። የሰው ልጅ ህይወቱን የሚለውጥለትን ነገር አይጠላም። ስለዚህ ሰዎች ልማት እንደጠሉ አድርጎ ማሰብም ማውራትም የውሸት ፕሮፓጋንዳ ነው። ወደ ጉዳዩ ስንመጣ ተማሪዎቹ ያነሱትን ጥያቄና በተማሪዎቹ ላይ እየደረሰ ያለውን ነገር እንይ።

ተማሪዎቹ ማስተር ፕላሉን በመቃወም በተለያዩ ዩኒቭርሲቲዎች ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው። ይሄ ሙሉ ለሙሉ መብታቸው ነው። አብረውም ሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ነው። ለምሳሌ: ኦሮምኛ ከአማርኛ ጋር አብሮ የፌደራል መንግስት የሥራ ቋንቋ ይሁንና የመሳሰሉት። ይሄም ሙሉ ለሙሉ መብታቸው ነው። ከዚያም አልፎ
ኦሮሚያ ትገንጠል ቢሉ እንኳን ይሄም ሙሉ ለሙሉ መብታቸው ነው። ማንም ሰው ለሌላ ሰው ይሄንን ብለህ ጠይቅ ወይም አትጠይቅ ብሎ አጀንዳ ሊያዘጋጅለት አይችልም። ይሄንን ማድረግ የሚፈልጉ አምባ­ገነኖች ብቻ ናቸው። እኔ ደግሞ አምባ­ገነኖች ከየትኛውም አቅጣጫ ቢመጡ አልቀበላቸውም። ዋናው ጉዳይ ተማሪዎቹ ጥያቄያቸውን በሰላማዊ