Sunday, April 13, 2014

ሕወሓት ከምርጫ 2007 በኋላ ጠቅላይ ሚ/ር ለመቀየር አስቧል – ሃይለማርያም ውጣ፤ ቴዎድሮስ ግባ?

ሕወሓት ከምርጫ 2007 በኋላ ጠቅላይ ሚ/ር ለመቀየር አስቧል – ሃይለማርያም ውጣ፤ ቴዎድሮስ ግባ?

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም አቶ መለስን ለመምሰል ቢሞክሩም፤ በሕወሓቶች ዘንድ ግን ማስመሰላቸው ሊዋጥላቸው አልቻለም
ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም አቶ መለስን ለመምሰል ቢሞክሩም፤ በሕወሓቶች ዘንድ ግን ማስመሰላቸው ሊዋጥላቸው አልቻለም

በሃገር ቤት የሚታተመው አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ እንደዘገበው ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) በሙስና ስም የ“ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ በመንግሥት ሥልጣን ላይ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮች መሐል ተከስቷል በተባለ አለመተማመንና መጠራጠር መስፈኑ ካድሬዎችን በእጀጉ እንዳስጨነቀ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ ለመመለስ በመቸገራቸው ብቻ በፓርቲውን ውስጥ ለመቆየት መወሰናቸውንም ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል።
ካድሬዎቹ ቀደም ሲል ኢህአዴግን ተሰናብተው ለወጡና በተለያዩ ግብረ ሠናይ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ለሚገኙ የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸው “በደህና ጊዜ ተገላገልክ” በሚል በፓርቲው ውስጥ ችግር ስለመኖሩ እየነገሯቸው መሆኑን የጠቀሰት የዜና ምንጮቹ፣ ለስራ ከሃገር መውጣት የማይችሉ ባለስልጣናት ጭንቀት ውስጥ መግባታቸውን ይናገራሉ። ለሃላፊዎቹ ደህንነት ሲባል የሚሰሩበትን ተቋምና ስም መናገር እንደማይችሉ በመጥቀስ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች “ባለስልጣኖቹ በመካከላቸው እርስ በርስ መተማመን በመጥፋቱ ችግራቸውን መወያየት እንኳን አይችሉም” ብለዋል፡፡
“በጣም የሚቀርቡኝ ጓደኞቼ ገንዘብ ወደ ውጪ እንድወስድላቸው እስከመጠየቅ ደርሰዋል” ሲሉ የገለጹት አነድ የቀድሞ የኢህአዴግ ባለስልጣን፣ ፓርቲው በሙስና ስም ያካሄደው የሽግግር ወቅት የማጥራት ርምጃ የፈጠረው ስሜት አሁን ድረስ እንዳለ ጠቁመዋል። ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ያቀኑ
የቀድሞ የኢህአዴግ አመራር “ኢህአዴግ በከፍተኛ የመበስበስ አደጋ ውስጥ ይገኛል። በዚህም የተነሳ ካድሬው ተዥጎርጉሯል” ሲሉ መናገራቸውም ተገልጿል።
Ethiopian regime’s foreign affairs minister Teodros Adhanom warns ENTC over Nile damይሕ በእንዲሕ እንዳለ የየኢሕአዴግ አባል ድርጅት የሆነው ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሐት) ከምርጫ 2007 በኋላ ለሁለት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሾሙትን ኃይለማርያም ደሳለኝን በውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቴዎድሮስ አድሃኖም ለመተካት እንቅስቃሴ መጀመራቸው በፓርቲው ውስጥ
ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርት መቅረቡ ተሰምቷል። ይኽው ሪፖርት የቀረበላቸው ክፍሎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት የህወሐትን ከፍተኛ አመራሮች በማነጋገር እየወተወቱ (ሎቢ እያደረጉ) መሆናቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል።
ምንጭ አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ (በሃገር ቤት የሚታተም)

No comments:

Post a Comment