Friday, December 27, 2013

ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊ እንሁን

      ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊ እንሁን

ይች ሃገር ያለመሪ ነው የምትመራው ብል ማጋነን አይሆንብኝም ምክንያቱም ህዝቦች ባላችው መቻቻል እና አብሮ የመኖር ፍቅር ሁሉን አቻችለው እንዲኖሩ አድርጝቸዋል ከሁሉ የሚገርመው መንግስት አንዱን ብሄር ከሌላው ሊያጋጭ የተቻለውን ሁሉ ሲያደርግ በየብሄሩ
ያሉ ምራቃቸውን ዋጥ ያደረጉ የሃገር ሽማግሌዎች ገና ከጥንስሱ ነገሩን ያመክኑታል ልጆቻቸውን እየገሩ ሃገር ማለት ምን ማለት  እንደሆነ እየመከሩ እያስተማሩ ያችን ሃገር  ሀገር ሆና እንድትቀጥል ላደርጉ ለነዛ የሃገር ባለውለታዎች ክብር እና ምስጋና ይሁን እንደ ወያኔዎች ሃሳብማ ገና ወንበር ከመያዛቸው ሃገሪቱ እንደ ሃገር አትቀጥልም ብለው ነበር ለዚህ ነው ሁሌ ሲያስፈራሩን ልትበጣጠስ አንድ ሳምንት የቀራትን ሃገር ከመከፋፈል አዳናት እያሉ ሊዘባነኑብን የሚፈልጉት።
       በመሰረቱ ያቺ ሃገር እንደ ሃገር ልትቀጥል የቻለችው ህዝቦች ባላቸው የዘመናት የመቻቻል ባህል ነው እንጂማ ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት የተሰሩብን ደባዎች እንኩዋን ለኛ አለምን ያስገረመ ነው በዓለም ታሪክ የራሱን ህዝብ በተቀናጀ ሁኔታ ያሸበረ የመጀመሪያው መንግስት ወያኔ ።  

ከላይ ያነሳሁት ሃሣባቸው አልሳካ ሲል ሰሞኑን ደግሞ ሌላ መርዶ ሊያሰሙን ደፋ ቀና እያሉ ነው 1200 ኪ ሜትር እርዝመት ያለውን ለም መሬት ለሱዳን ለመስጠት እና የራሳቸውን የአየር ድንበር ለማበጀት መሪ ብለው ባስቀመጡት አሻንጉሊት አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ
ህዝብ ሣያውቅ እንደ ወንበዴ ውስጥ ለውስጥ ስምምነት ላይ ለመድረስ ከጫፍ ደርሰዋል 

Thursday, December 26, 2013

ያ ትውልድ እና እኛ

                      ያ ትውልድ እና እኛ

 እኔ ማለት የዘመን ክስተት ነኝ የሚገርመኝ ልጅነቴን ሳላውቀው እንደሸኘሁት
 ሁሉ ወጣትነቴም ለጎልማሣነት አሣልፍ ሊሰጠኝ ከጫፍ ያደረሰኝ ሰው ነኝ

 ሁሌም የሚገርመኝ እና የሚደንቀኝ ነገር ስለምን ያ ትውልድ አልፉታን አለ
 በራሱ የሚተማመን የራሱን አብዬት ሊያስነሳ የሚችል የሀገር ፍቅር ስሜት
 ከውስጡ የሚፍለቀለቅ ትውልድ ስለምን መሆን አቃተን እንዴትስ በሁሉም አቅጣጫ
 ያ ትውልድ ስለምን ተቆጣጠረን የሚለው የዘወትር ጥያቄዬ ነው

Sunday, December 8, 2013

ልማት ወይስ ስጋት ?

         
             ልማት ወይስ ስጋት ?


ወያኔ-ኢሕአዴግ ያገሪቱን የኢኮኖሚ አውታር በሰፊው በመቆጣጠር፣ በዙሪያው ለተሰባሰቡ የጥቅም አጋሮቹ
የማየርነጥፍ የሃብትና የንዋይ ጎተራ ሆኖላቸዋል፡፡ ሰፊው ሕዝብ የእለት ጉርስ አሮበት፣ መታከሚያ ቸግሮት፣ ፍትህና ርትእ ርቆት በችግር በሚጉላላበት ሰአት፣ ወያኔና አሽከሮቹ በድሎት እየተንደላቀቁ ሕዝብ ላይ ማግሳት ከጀመሩ ከ21 አመታት በላይ ሆኗል፡፡ በዚህም አገሪቱ በጥት ጠመንጃ ነካሽ ያገር ጠላቶች እጅ ወድቃ በመማቀቅ ላይ ትገኛለች፡፡

አገራችን በእንዲሀ አይነቶቹ የቀን ጅቦች መዳፍ ስር ወድቃ ወዴትም ልትራመድ የማትችል በመሆንዋ ቀጣ እጣ ፈንታዋ ሁሌም አሳሳቢ ሁኖ ይቀጥላል፡፡  የሀገሪቱን ቀጣይ ሂደት ወቅታዊውን የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የማህበራዊ እድገት የሚያቀጭጭ ብቻ ሳይሆን፤ በሀገሪቱ ታሪካዊና ብሄራዊ ኩራቶች ላይ ሁሉ ትልቅ ስጋት የሚደቅን ነው፡፡ ይህ በጠመንጃ ላይ የተመሰረተ የግፍ አገዛዝ፣ ከአለማቀፉዊ የመረጃ ፍሰትና የንቃተ ህሊና
እድገት ጋር በፍፀም ሊጣጣም የማይችል ነው፡፡ የሰውን ልጅ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በዘመናዊ ባርነት ቀንበር ስር ለመግዛት የሚያደርገው ጥረት ባጭሩ መቀጨት ያለበት ነው፡፡

Thursday, December 5, 2013

ስሟ በውቅያኖስ ተሰይሞላት እንዳልነበር


ስሟ በውቅያኖስ ተሰይሞላት እንዳልነበር

ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ታሪክ ባለቤት ናት ሲባል አንዳንድ ኢትዮጵያዊ እንዲሁ ሀገራችንን ስለምንወድ ብቻ የሚወራ ይመስለው ይሆናል። እውነቱ ግን ይሄ አይደለም፡፡ በእውነትም አገራችን የሚያኮራ ታሪክና ገድል ያላት ጥንታዊት አገር ነች፡፡
ባንድ ወቅት የደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ ኢትዮፒክ ውቅያኖስ ይባል እንደነበር ስንቶቻችን እናውቅ እንደሆነ አይታወቅም፡፡ ይሄ እድሜ ጠገብ ውቅያኖስ በእርግጥም የደቡቡ ክፍል “ኢትዮፒክ ውቅያኖስ” ይባል እንደነበር የታሪክ ተመራማሪዎች ያሰምሩበታል፡፡ ይህ ደቡባዊ ያትላንቲክ ውቅያኖስ ክፍል እስከ አስራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ባገራችን ስም ስያሜ ይጠራ እንደነበርም ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

ይህን ለምሳሌ ያህል በመጥቀስ ያንድ ወቅት ታላቅ ሕዝብና አገር ባለቤቶች እንደነበርን ለማሳየት ሞከርኩ እንጂ፤ የኢትዮጵያን ታላቅነት በዝርዝር ማሳየት ካስፈለገ ብዙ ሌሎች ምሳሌዎችን መጨመር ይቻላል፡፡ ኢየሩሳሌም ያሉትን ገዳማት ጨምሮ ባገራችን ያሉ ብዙ ጥንታዊ ገዳማት፣ አብያተ ክርስቲያናት ታሪካዊ ስፍራዎች እንቁ ጌጦቻችንና መታወቂያችን ናቸው፡፡  በወርቃማው የፈርኦን ዘመን እኩል ሥልጣኔ የነበረን ታላቅ ሕዝቦች እንደ ነበርን፤ ያክሱም ሐውልት ቋሚ ሕያው ምስክር ነው፡፡ የላሊበላ ውቅር አብያት ክርስቲያናት፣ የጎንደር ቤተ መንግስቶች፣ የሶፍ ኡመር ዋሻና የመሳሰሉት ድንቅ የታሪክና የተፈጥሮ ቅርሶቻችን መኩሪያዎቻችን ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ አገራችን የአፍሪካ የነፃነት ምልክትና አርማ እንዳልነበረች ሁሉ፤ ዛሬ በኛ ትውልድ ዘመን፤ ፔትሮ ዶላር ያሰከራቸው አረቦች መቀለጃና መጫወቻ ሆናለች፡፡ ለዚህ ደሞ ማረጋገጫው በቅርቡ በሳውዲ አረቢያ መንግስትና ወሮበሎች አማካኝነት በዜጎቻችን ላይ የደርሰው ውርደትና ስቃይ ነው፡፡ ዜጎቻችን ተገለዋል፣ ታስረዋል፣ ተቀጥቅጠዋል፣ ተዘርፈዋል፣ ተደፍረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከዚህ የበለጠ በደልና ውርደት በታሪኳ ውስጥ አይታይም ሰምታም አታውቅም፡፡

የወያኔ ሹማምንት ከድሃ ሕዝባችን ላይ እየዘረፉ በውጭ ባንኮች ውስጥ ያከማቹትን ገንዘብ የትየለሌ ሆኗል፡፡ ለዚህ ምሳሌው የነአዜብ ጎላና የመሳሰሉት የውጭ ባንክ ገንዘብ ክምችት ነው፡፡ ድሮ በነቢልጌት የገንዘብ መጠን እንደመም እንዳልነበረ ሁሉ፤ ዛሬ ደሞ በራሳችን ብር ጌቶች በነአዜብ ቱጃርነት መደመም ጀምረናል፡፡

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ፤ ዛሬ መሬታችን ለውጭ ባለሀብቶች እየተቸበቸበ፣ ሕዝባችንን ጦም አዳሪ ያደረገ የወያኔ አስከፊ ስርአት አለ፡፡  ባለመሬቱ ያገር ሰው እይተፈናቅል እነካራቹሪና አረብ ቱጃሮች እርስቱን የመበዝበዣ መሳሪያ አድርገውታል፡፡ የሳውዲ እስታር የተባለው ኩባንያ አገራችን ውስጥ ትልቅ የርሻ ቦታ ይዞ የኛን ዜጎች ደሞ የገላል፣ ያስራል፣ ይዘርፋል፣ ይደፍራል….

የወገኖቻችንን ጉዳት የተመለከተው የአዲስ አበባ ህዝብ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጣበት ጊዜ፤ መንግስት ተብዬው ሰልፉን አግዶ ካረቦቹ ጎን ተሰለፈ፡፡ ይሄኔ ነው ባገር ቤትም በውጪም ያለነው ሁሉ፣ ለዚህ ውግናችን ማን ይድረስለት ማን ያስጥለው ከጅቦቹ እያልን ጩኸት የጀመርነው፡፡  

 ኢትዮጵያ የታሪክ ባለሀብት ብቻ አይደለችም፡፡ አሁንም ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ብናየው
እንዃን የብዙ ሙህራን ባለቤት ናት ። የሀገራችን የሰብአዊ መብት ጥሰት ሁኔታ አስገድዶቸው
አብዛኞቹ ከአገራቸው ተሰደው ባእድ አገርን እያገለገሉ የሚኖሩ ይገኛሉ።  የአገራቸው
ጥፋትና ጉዳት ውስጣቸውን እየበላ በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለሚመለከተው ክፍል ያስታዉቃሉ፣ የጮሃሉ፣ ይታገላሉ… ከዚህም በተጨማሪ በሀገር ፍቅር ናፍቆት ውስጣቸው እየተቃጠለ የሚሰቃ ብዙዎች ናቸው።

እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ በላይ ውርደትን ለመቀበል ህሊናችንን ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ በኳስ ላይያሳየነውን አንድነት ግማሹን እንኳን አምባገነኖችን ለማስወገድ ፋይዳ ብንጠቀምበት፤ የደስታችንን ምንጭ በራሳችንን እጅ እንደጨበጥን ይቆጠረ ነበር፡፡ ስለዚህ ህብረታችንን
ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ማጠንከር ይኖርብናል፡፡የዚህችን ታሪካዊ ሀገር ክብር የማስመለስ

ብሔራዊ ግዴታ እሁላችንም ዘንድ አለና መጠንከር አለብን ።

                                                 ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር


ከምናሴ መስፍን
ከኖሪቤ ኦስሎ