Monday, May 16, 2016

                             What if I Covet the Norwegian 17th of May?

Norway is a free independent democratic kingdom. The nation’s constitution was penned in 1814 in an effort to free the country from the foreign domination 202
years a go.
 Being inspired by a great zeal and love of their country; based on the then great interest and need of the nation; as much as the scope of their knowledge allowed them some 120 Norwegian nationalists came up with such an amazing work.
 Being the second largest in the world, this constitution officially called “Kongeriket Norges Grunnlov” was first adopted on May 16 and subsequently signed and dated on 17 May 1814 by the Norwegian constituent Assembly at Eidsvål. Since then, the day 17th May is being celebrated as a national day indicating that Norway is a sovereign state.
 The constitution was not formed and or created to serve the few parliament members or the ruling organ. Rather, it was to magnify the nations freedom and to keep it’s democratic right and uphold the peoples sovereignty. In addition to that, it was related it’s character, to the international democratic rules and laws as general.
 

Wednesday, February 25, 2015

እነ ማን ነበሩ? አሁንስ ማን ናቸው?


ገብረመድህን አርኣያ
ፐርዝ፤ አውስትራሊያ

ይህ ጽሑፍ ትኩረት የሚሰጠው በትግል በረሃ በነበርንበት ወቅት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት.) በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖቶች ላይ ሲከተል የነበረውን አቋሙን ተቀብሮ ከነበረበት ጉድጓድ አውጥቼ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እነማን ናቸው የሚለውን ታሪካቸውን እና የተፈጸመውን ጸረ-እምነት ግፍ በአጭሩ ለማሳወቅ ነው።

ህ.ወ.ሓ.ት. ገና ሲፈጠርና ተ.ሓ.ህ.ት. ተብሎ እንደተመሰረተ ሙልጭ ያለ ጸረ-ዲሞክራሲ ድርጅት ነው። በጸረ-ኢትዮጵያነትና በጸረ- ሕዝብነት የተሰማራ ቅጥረኛ ድርጅት መሆኑን ብዙ ጊዜ በጽሑፍና በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ለኢትዮጵያ ህዝብ ተናግሬአለሁ። የአሁኑ ጽሑፌ ህ.ወ.ሓ.ት. በሃይማኖት ላይ ሲከተለው የነበረውን ፖሊሲ ገና ከመጀመሪያ ትግሉ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ የነበረውን ጸረ- ሃይማኖት ተግባራቱን የኢትዮጵያ ሕዝብ በግልጽ አውቆታል። እኔ ደግሞ የራሴን ልበል።

በ1969 መጀመሪያ ጀምሮ “ወይን” በሚለው የድርጅቱ ልሳን መጽሔት ላይ በተደጋጋሚ “የክርስትና ሃይማኖትና አማራው” በሚል ርእስ ተጽፎ የሚወጣው ጽሑፍ፣ “የክርስትና ሃይማኖት የአማራው ዋና መሳሪያና የግዛቱን ህልውና ማስጠበቂያ ነው፣ በመሆኑም የትግላችን ጠላት አማራውና መሳሪያው የተዋህዶ ክርስትና ስለሆኑ አብረው እንዲጠፉ  ማድረግ አለብን” እያለ ያትት ነበር። ይህንን መጽሔት በሰፊው ለታጋዩና ለአባላቱ በማሰራጨት ሰፊ ቅስቀሳ አካሂዶበታል። በነሐሴ 1969 “ወይን” መጽሔት አማርኛ ቋንቋም አብሮ መጥፋት እንዳለበት ሃተታ ይዞ ወጥቷል።

Tuesday, February 17, 2015

እየከፋ በመጣው የሰብአዊ መብት ረገጣ ላይ የጋራ አቋም መግለጫ ከፖለቲካ ፣ ሲቪክ ፣ የሃይማኖት ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች

«ለውጥ በማይቆም ተሽከርካሪ የሚጓዝ አይደለም፤ የተከታታይ ትግል ውጤት ነው። ነጻነት የምንፈልግ ሁሉ ጀርባችንን ቀና አድርገን መታገል አለብን። ራሳችን ካልፈቀድንለትና ካልተሸማቀቅን፤ ማንም ሰው እንደ ከብት ሊጋልበን ከቶ አይችልም” ነበር ያሉት ዶር ማርቲን ሉዘር ኪንግ ጁኔር ።

በማንኛውም አገር ቢሆን፣  ነጻ የሆነ የዜና አገልግሎት የማያገኝ፤ ተቆርቋሪ የፖለቲካ ወይንም የማህበረሰብ ወይንም የሲቪክ ድርጅት እና በነጻነት የሚንቀሳቀስ የመገናኛ ብዙሃን አገልግሎች የሌለው  ሕዝብ መብት የለውም። መብቱ በመንግሥት የተከለከለ ግለሰብ ሆነ ቡድን፤ ማህበረሰብ ሆነ ሕብረተሰብ ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው እድገት አይጎናፀፍም።


ሕወሃት/ኢሕአዴግ ለሃያ አራት ዓመታት በበላይነት ሲገዛት የቆየችዋ ኢትዮጵያችን  ፍትህ፤ ነጻነት፤ ሰብአዊ መብት፤ የሕግ የበላይነት  የማይታይባትና  አምባገነናዊ ስርዓት የሰፈነባት ሃገር ሆናለች። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ የመድበል ፓርቲ ስርዓት የምትከተል መሆኗ በሕግ መንግስቱ ቢደነገግም፣ በተግባር የታየው ግን ከገዝው ሕወሃት/ኢሕአዴግ ነጻ የሆኑ ድርጅቶችን ሁሉ የማጥፋት ሂደት ነው። የአገሪቷን ሕግ ሆነ የምርጫ ቦርድን አሰራር  በጣሰ መልኩ፣ በቅርቡ በአገሪቷ ጠንካራ የሚባለውን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)  አመራርን በማገድ ራሱ ያቋቋማቸዉን ተለጣፊ መሪወች መሾሙ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ  በምርጫ የማያምንና፣ ብቻውን ለሚቀጥሉት ሃያ፤ ሰላሳ አመታት በጉልበት ለመግዛት እንደወሰነ አመላካች ነው። የዜጎችን የመደራጅትና የመሰባሰብ ሰባአዊ መብትም የረገጠ ነው።

Monday, February 16, 2015

‹‹ሰላማዊ ትግሉ ሲጠናከር ስርዓቱ ወደ አውሬነት ይቀየራል›› ‹‹ቃል ኪዳናችንን ማጥበቅ አለብን!›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት


‹‹ሰላማዊ ትግሉ ሲጠናከር ስርዓቱ ወደ አውሬነት ይቀየራል››
‹‹ቃል ኪዳናችንን ማጥበቅ አለብን!››
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
(በዛሬው ዕለት ለቀድሞው የአንድነት አመራሮችና አባላት የተዘጋጀው የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ላይ ከተናገሩት)
ፓርቲ ጣኦት አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ቅንጅትንም አፍርሶታል፡፡ አንድነትንም አልፈረሰም ብለው እንዳይከሱኝ እንጅ አፍርሰውታል ማለት እችላለሁ፡፡ በዚህ ሁኔታ ሰማያዊ ላይም አንድ ነገር ማምጣታቸው የማይቀር ነው፡፡ ያ ማለት ግን ሰላማዊ ትግሉ ምን ያህል እንዳስፈራቸው ነው የሚያሳየው፡፡ አገዛዙ በፓርቲዎች ላይ የሚወስደው እርምጃ የሚያሳየው ሰላማዊ ትግሉ መጠናከሩን እንጅ ወደኋላ መመለሱን አይደለም፡፡ አንዳንዶቹ እንዲህ አይነት ችግር ሲከሰት ሰላማዊ ትግሉ አበቃለት ይላሉ፡፡ ሆኖም አገዛዙ ሰላማዊ ትግል አስፈርቶት አውሬ ሲሆን የሚያረጋግጥልን ሰላማዊ ትግሉ መጠናከሩን ነው፡፡
Blue Party
በመሳሪያ ትግል ውስጥ አንድ ጀኔራል ሲሞት አሊያም አንድ የጦሩ አካል ችግር ሲደርስበት ‹‹የትጥቅ ትግል አበቃለት›› እንደማይባለው ሁሉ ሰላማዊ ትግል ላይ አንድ ጫና ወይንም የስርዓቱ ደባ ሲከሰት ትግሉ አይሰራም ማለት አይደለም፡፡
ሰላማዊ ትግል መስዋዕትነት አያስከፍልም ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ሰላማዊ ትግል ውጤት ማምጣት ሲጀምር፣ ዙሩም ሲካረር፣ የሚከፈለው ዋጋም ይበልጥ እየጨመረ ይሄዳል፡፡ የስርዓቱ አውሬነት በተገለጠ ቁጥር፣ እኛም በተሻለ አመራር ትግሉን ስንመራው መስዋዕትነቱ ይበልጡን እየበዛ እንደሚመጣ እንረዳለን፡፡

Sunday, February 15, 2015

የምርጫ ሂደቱ በኢህአዴግና በምርጫ ቦርድ ከፍተኛ ችግር እየደረሰበት ነው! ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ሰማያዊ ፓርቲ በ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ ተወዳድሮ በማሸነፍ የመንግስትን ስልጣን ለመያዝ የሚያበቃውን ውጤት ለማስመዝገብ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫውን ነፃና ፍትሀዊነት ለማረጋገጥ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በጋራ በመሆን ነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ የሚል መርሀ ግብር በማዘጋጀት ምርጫ ቦርድን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት ነፃና ገለልተኛ እንዲሆኑ በተለያዩ መንገዶች ጥያቄዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ እስካሁን ከተደረጉት እንቅስቃሴዎችም በተጨማሪ ምርጫ ቦርድና የመንግስት አስፈፃሚ ተቋማት በህገ መንግስቱ በተደነገገው መሰረት ነፃና ገለልተኛ ሆነው እንዲሰሩና የፖለቲካ ምህዳሩም ለሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ፍትኃዊ እሰኪሆን ድረስ የነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ ዘመቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በሁሉም የሀገሪቷ ክፍሎች እጩ ተወዳዳሪዎችን ለማስመዝገብ ባደረጋቸው እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የምርጫ አካባቢዎች በዕጩ ተወዳዳሪዎቻችን ላይ በገዢው ፓርቲ አባላትና በምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች ከፍተኛ እንግልትና እንቅፋት የተፈጠሩባቸው ሲሆን ለአብነት ከብዙ በጥቂቱ ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡



1. በተለያዩ አካባቢዎች ላይ እጩ ተመዝጋቢዎች የተወለዱበት ዞን መሆኑ እየታወቀ ነገር ግን ምስክር አምጡ በማለት እንዳይመዘገቡ ተደርገዋል፡፡

2. በሰሜን ጎንደር ዞን ባሉ ወረዳዎች በሙሉ የምርጫ አስፈፃሚዎች ፅ/ቤቶችን ዘግተው በመጥፋታቸው ምክንያት መመዝገብ በተደጋጋሚ የሄዱ እጩ ተመዝጋቢዎች ሳይመዘገቡ ጊዜው እንዲያልፍባቸው ተደርገዋል፡፡

Tuesday, February 3, 2015

ወያኔ ‘ታላቋን ትግራይ’ ለመመስረት ‘crime against humanity’ ና ‘genocide’ በመፈጸም ላይ ነው

ይህ ፅሁፍ የሚያተኩርበት ዋና ጉዳይ ወያኔ ‚ታላቋን ትግራይ‛ ተብላ የምትጠራ አገር ለመመስረት ሲል በጎንደርና በወሎ ህዝብ ላይ የፈጸመውንና አሁንም እየፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት(genocide) እና ትግራይ ያልሆነ ህዝብን ማፈናቀሌ (ethnic cleansing) ወንጀልች ሊይ ነው። በመላ ኢትዮጵያ የሚደረገውን የኢኮኖሚ ገፈፋና በየትኛውም የመንግስትና የግል የኑሮ ዘርፎች የትግራይ የበላይነት ለማረጋገጥ ሲባል ወያኔ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ የሚያካሂደውን የሽብር ዘመቻ የዚሁ መሰሪ አላማ አካል ነው። ከዚያ ባሻገር ጎጠኛ አስተዲደር (ethnic federalism) እና የመገንጠል አንቀጽ (አንቀጽ 39) የተባለት አንኳር የወያኔ መርሆች አገልግሎታቸው ወያኔ እንደሚለፍፈው የብሔሮችን እኩልነት ለማረጋገጥ ሳይሆን ሌሎች ብሔሮችን በማፈናቀልና በማራቆት የትግራይ ክልልና የትግራይ ተወላጆች ሀብት እንዱያካብቱና ለሚመሰርቷት ታላቋ ትግራይም ስትራቴጂካዊና ውሀ ገብ ለም መሬቶችን ለመንጠቅ እንዲያመቸው ያስቀመጣቸው ለመሆናቸው ይህ ጽሁፍ አባሪ መረጃዎች ያቀርባል። ወያኔ በጎንደርና በወሎ ህዝብ ላይ የሚፈጽማቸው ወንጀሎች በግብታዊነት የተከሰቱ ሳይሆን ለረጅም ጊዜ በተጠና እቅድ መሰረት ነው።

ወንጀሎቹ ከሞላ ጎደል የሚከተለው ቅደም ተከተል አላቸው።

1. ለምና ስትራቴጂካዊ (strategic) የሆኑ ቦታዎችን ትግራይ ካልሆኑ ህዝቦች በመንጠቅ በትግራይ ክልል ስር እንዲጠቃለሉ ማድረግ፤

2. በተነጠቁ ቦታዎች ላይ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎችን ማስፈር፤ ከትግራይ ክልልና ከማእከላዊ የወያኔ መንግስት በሚለገስ ገንዘብ አማካኝነት አዲስ የትግራይ ሰፋሪዎችን ሀ) ማስታጠቅ፣ ለ) በእርሻና በሌላ የልማት መስኮች ማደርጀት፤

3. በአዱስ ታጣቂ ሰፋሪዎች አማካኝነትም በነባሩ ህዝብ ሊይ የማፈናቀልና የማሳደድ ዘመቻ በመክፈት አካባቢውን የትግራዮች ብቸኛ ሀብት ማድረግ፤

4. መስፋፋቱንና በሃይል መፈናቀሉን በቆራጥነት የሚቃወሙትንና በነዋሪው ህዝብ ዘንድ ተሰሚነት አላቸው የሚሏቸውን ግለሰቦችን ማፈን፣ ማሰርና መግደል፤ የቀሩትን ሰዎች በማንገላታት ቢቻል ክልሉን ለቀው እንዲሰደዱ ማዴረግ ካልተቻለ ደግሞ ለምነት በሌላባቸው መሬቶች ተጨናንቀውና ተጣበው እንዲታሰሩ በማዴረግ ለከፍተኛ ችግርና ረሀብ እንዱጋለጡ ማድረግ፤

5. የኗሪውን ህዝብ የደረሱ ልጃገረዶች በትግራይ ጎረምሳ ኮርማዎች ማስደፈር፤ (rape ማስደረግ)፤ በዚህ ባህልን፣ ሃይማኖትንና ሰብአዊነትን ባዋረደ ተግባር የትግራይ ዘር ያላቸውን
ልጆች እንዲወልዱ ማድረግና ከዚያ በበለጠ ደግሞ ሌላ ትግራይ ያልሆኑ ወላጆችንና ወንድ ወጣቶችን ቅስም መስበር ነው።

Saturday, January 31, 2015

የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ኖሮ አያውቅም

የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ኖሮ አያውቅም

(ecadforum.com ኢዲቶሪያል)

ሰሞኑን ወያኔ/ኢህአዴግ በህግ ተመዝግበው በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶችን ለማጥፋትና በመጪው ምርጫ ላይ እንዳይሳተፉ ለማድረግ በርትቶ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።


እስካሁን መኢሕአድ እና አንድነት ፓርቲ የዚሁ የወያኔ/ኢሕአዴግ የቅድመ ምርጫ “ተቃዋሚዎችን የማዳከም እና የማጥፋት ዘመቻ” ሰለባ ሆነዋል።


በቅርቡ ራድዮ ፋና እና ኢቲቪ ከሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ጋር አድርገውት የነበረውን ቃለ-ምልልስ (በኋላ የቃለ-ምልልሱ ድምጽ ጠፋብን ማለታቸው ይታወሳል፣ ይሁንና ኢሳት ቴሌቪዥን ጠፋ የተባለው ቃለ-ምልልስ በእጁ ገብቶ ኖሮ እያሰራጨው ይገኛል) ቃለ-ምልልሱን ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ። ከቃለ-ምልልሱ መረዳት እንደሚቻለው ፖሊስ ቀመሱ የወያኔ/ኢሕአዴግ ጋዜጠኛ ምን ያህል ሰማያዊ ፓርቲን የሚያስወነጅሉ ነገሮች ፍለጋ ይባዝን እንደነበር ነው። ይህ የሚያመለክተው ሰማያዊ ፓርቲ ቀጣዩ የወያኔ/ኢህአዴግ “ተቃዋሚዎችን የማዳከም እና የማጥፋት ዘመቻ” ሰለባ እንደሚሆን ነው።

ወደ ተነሳንበት ርዕስ ስንመለስ፣ ከላይ የተጠቀሱትን ሁነቶች ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ አንዳንድ በተቃውሞ ጎራ የተሰለፉ ፖለቲከኞች እና ለውጥ አራማጆች “ወያኔ/ኢሕአዴግ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትን እያቀጨጨ ነው፣ ገዢው ፓርቲ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትን እያጠፋ ነው፣ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት አከተመለት…” ሲሉ ይደመጣሉ።